Newtenderethiopia

ኢትዮጵያ በ34 ሚሊዮን ዶላር አዲስ ተሽከርካሪዎችን ልትገዛ መሆኗን አስታወቀች

ኢትዮጵያ በ34 ሚሊዮን ዶላር አዲስ ተሽከርካሪዎችን ልትገዛ መሆኗን አስታወቀች

የቻይና ሶስት ኩባንያዎች 312 ተሽከርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ለመሸጥ ተስማሙ የቻይናዎቹ ዞሆንግቶን ሻንዚ እና ሻንጋይ የተሰኙ የአውቶሞቲቭ ኩባንያዎች ኢትዮጵያ ተሽከርካሪዎችን ለመግዛት ያወጣችውን ዓለም አቀፍ ጨረታዎችን አሸንፈዋል ተብሏል። ኢትዮጵያ ለተሽከርካሪዎቹ ግዢ 34 ሚሊዮን ዶላር በጀት መመደቧ ተገልጿል። የመንግስት ግዥ አገልግሎት በገንዘብ ሚኒስቴር ጠያቂነት ለፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች እና ለመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አገልግሎት የሚውሉ ተሽከርካሪዎችን ለመግዛት ጨረታ አውጥቶ ነበር። ሊገዙ የታሰቡት ተሽከርካሪዎች ብዛታቸው 312 ሲሆኑ በኤሌክትሪክና በነዳጅ የሚሰሩ እንደሆኑም ተገልጿል። ለተሽከርካሪዎች ግዢ 34 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላር ወጪ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 33ቱ የኤሌክትሪክ ሚኒባስ ናቸው ተብሏል። የቻይናው ዞሆንግቶን የተሰኘው ኩባንያ 47 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሚኒባሶችን በሶስት ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ ለማስረከብ ጨረታውን እንዳሸነፈ ተገልጿል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ለረዥም ጊዜ ተቋርጦ የቆየውን የአደይ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመት እንደገና ለማስጀመር በጀት መያዙን ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ገልጿል ። የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በ48 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባውና 62ሺ ተመልካች የመያዝ አቅም ያለው ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታን ለማስቀጠል በ2016 ዓ.ም በጀት የተያዘለት በመሆኑ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ ግንባታው ይጀመራል። የብሔራዊ ስታዲየሙ ግንባታ በቻይናው ኩባንያ ይካሄድ እንደነበረ አስታውሰው፤ ግንባታው በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱን ገልፀዋል። በኋላም የግንባታ ተቋራጩ ለሥራው ያቀረበው የዋጋ ማስተካከያ ከገበያ በላይ የተጋነነ በመሆኑ መንግሥት ከያዘው በጀት ጋር ሊመጣጠን አልቻለም። በዚህም ከግንባታ ተቋራጩ ጋር ያለው ውል እንዲቋረጥ መደረጉን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።…
Read More