carimporting

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመቀየር ጥናት እየተደረገ  መሆኑን የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወርቁ ደስታ እንዳሉት  "በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ባለው የአዲስ አበባ ኮሪደር ልማት በመኪና ማቆሚያዎች የኃይል መሙያ እየተሠራ ነው " ብለዋል።የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በበኩላቸው "ከዚህ በኃላ የተሽከርካሪ አስመጪና የሚገጣጥሙ ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የኃይል መሙያ ሳይተክሉ በሥራ ላይ መሰማራት አይችሉም " ብለዋል።በኢትዮጵያ ከ400 በላይ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እያስመጡና እየገጣጠሙ ነው የተባለ ሲሆን ሁሉም አስመጪዎች እና ገጣጣሚዎች የኃይል መሙያ እንዳላቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከአንድ ሳምንት በፊት  ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ማዘጋጀቷ…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እንዳያስገቡ እገዳ ጥላለች፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ዲፕሎማቲክ እና ሚሲዮኖች የነዳጅ መኪናዎችን እንዳያስገቡ እገዳ የጣለች ሲሆን በምትኩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስመጣት ብቻ እንዳለባቸው አሳስቧል። የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ እና የቆንስላ ሚስዮኖች፣ ለቀጠናው እና ለአለም አቀፍ ድርጅቶች በፃፈው ደብዳቤ " የተወሰደው እርምጃ ኢትዮጵያ የበካይ ጋዝ ልዕቀት ቅነሳና ወደ ታዳሽ ኃይል ለመሸጋገር ካላት ቁርጠኝነት የተነሳ መሆኑን" አስረድተዋል ። በዚህም የዲፕሎማሲ መብት ያላቸው ሁሉ ተሽከርካሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ የተሰጠውን አቅጣጫ አክብረዉ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ብቻ ማስመጣት ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ኢትዮጵያ ከመጋቢት 2016 ዓ.ም ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

በቻይና የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ማገዷን አስታውቃለች፡፡ በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ የሚገኘው ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሕጋዊ የሆነ ፈቃድ አለመኖሩን የጀርመኑ ኩባንያ በኤንባሲው በኩል በደብዳቤ ለሚኒስቴሩ ማሳወቁ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ሕጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስከሚረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ክትትል በማድረግና የሕጋዊነት ማረጋገጫ መረጃዎችን የማጥራት ስራም በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሠራ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት እንዲመረቱ፣ እንዲገጣጠሙና ወደ ሀገር…
Read More