Carmarket

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ የሌላቸው ድርጅቶች መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳያስገቡ ከለከለች

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ነዳጅ ማደያዎችን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመቀየር ጥናት እየተደረገ  መሆኑን የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ወርቁ ደስታ እንዳሉት  "በሁለተኛው ምዕራፍ እየተከናወነ ባለው የአዲስ አበባ ኮሪደር ልማት በመኪና ማቆሚያዎች የኃይል መሙያ እየተሠራ ነው " ብለዋል።የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ዴዔታ በርኦ ሀሰን በበኩላቸው "ከዚህ በኃላ የተሽከርካሪ አስመጪና የሚገጣጥሙ ድርጅቶች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የኃይል መሙያ ሳይተክሉ በሥራ ላይ መሰማራት አይችሉም " ብለዋል።በኢትዮጵያ ከ400 በላይ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ እያስመጡና እየገጣጠሙ ነው የተባለ ሲሆን ሁሉም አስመጪዎች እና ገጣጣሚዎች የኃይል መሙያ እንዳላቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ከአንድ ሳምንት በፊት  ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ማዘጋጀቷ…
Read More
ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ያሉ የዲፕሎማሲ ተቋማት በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖችን እንዳያስገቡ ከለከለች

ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም የዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እንዳያስገቡ እገዳ ጥላለች፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ የሚገኙ ሁሉም ዲፕሎማቲክ እና ሚሲዮኖች የነዳጅ መኪናዎችን እንዳያስገቡ እገዳ የጣለች ሲሆን በምትኩ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማስመጣት ብቻ እንዳለባቸው አሳስቧል። የዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ እና የቆንስላ ሚስዮኖች፣ ለቀጠናው እና ለአለም አቀፍ ድርጅቶች በፃፈው ደብዳቤ " የተወሰደው እርምጃ ኢትዮጵያ የበካይ ጋዝ ልዕቀት ቅነሳና ወደ ታዳሽ ኃይል ለመሸጋገር ካላት ቁርጠኝነት የተነሳ መሆኑን" አስረድተዋል ። በዚህም የዲፕሎማሲ መብት ያላቸው ሁሉ ተሽከርካሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ የተሰጠውን አቅጣጫ አክብረዉ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ብቻ ማስመጣት ይጠበቅባቸዋል ብሏል። ኢትዮጵያ ከመጋቢት 2016 ዓ.ም ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ…
Read More
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች ላይ የተጣለውን እገዳ ተቃወመ

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መከልከል ባለሃብቶችንና የውጭ ኢንቨስትመንቶችን ይጎዳል በማለት ተቃውሟል፡፡ ኮሚሽኑ ለትራንስፖርት ሚንስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ የሕግ ድንጋጌ ሳይኖርና ግልጽ ሕግ ሳይወጣለት ከበላይ አካል በተሰጠ ትዕዛዝ ብቻ ነዳጅ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ ማገድ አግባብነት የለውም በማለት ቅሬታውን እንደገለጠ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የተላለፈው ውሳኔ በግብርና፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር፣ በአበባ እርሻ ልማት፣ በቱሪዝም፣ በማኑፋክቸሪንግና ግንባታ እና ሌሎች ስራዎች በተሠማሩ ባለሃብቶች እና ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ መፍጠሩን ኮሚሽኑ አስታውቋል። ኮሚሽኑ አክሎም ለአንዳንድ ኢንቨስትመንት ስራዎች ከባሕሪያቸው አንጻር በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዲያስገቡ እንዲፈቀድላቸው ሲል እንደጠየቀም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ካሳለፍነው መጋቢት ወር ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር የስድስት ወራት ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሚኒስትሩ አቶ አለሙ ስሜ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ የሚደረገው ክልከላ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ አቶ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ለፓርላማው እንደተናገሩት፥ ነዳጅ የሚወስዱ ተሽከርካሪዎችን ለግል ጥቅማጥቅ ሆነ ለሌላ አላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚደረገውን እገዳ በጥብቅ እንደሚያስፈጽሙ ገልጸዋል። ውሳኔው ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ስጋቶች እና ከባህላዊ የነዳጅ ፍጆታ ጋር ተያይዞ እየጨመረ ለሚመጣው ወጭ ስልታዊ ምላሽ ነውም ተብሏል። እየጨመረ የመጣው የነዳጅ ወጪ ፖሊሲ አውጪዎች አገሪቱ በተለመዱት ተሽከርካሪዎች ላይ ያላትን ጥገኝነት እንዲገመግሙ እና የካርበን በካይ ጋዝ መጠንን ለመቀነስ ከሚደረገው…
Read More
ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ የፋው ምርት የሆኑ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ገበያ አቀረበ

ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ የፋው ምርት የሆኑ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ገበያ አቀረበ

የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ኢትዮጵያ ገበያዎች በማምጣት የሚታወቀው ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ አሁን ደግሞ የጭነት ተሽከርካሪዎችን ማስመጣቱን ገልጿል። ኩባንያው የቻይናው ፋው ሰራሽ የሆኑ የተለያዩ መጠን የመጫን አቅም ያላቸው አነስተኛ፣ መካከለኛ እና ከባድ እቃዎችን ሙጫን እሚችሉ የጭነት ተሽከርካሪዎችን አስመጥቷል። ፈርስት አውቶሞቲቭ ዎርክስ ወይም ፋው በመባል የሚታወቀው የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ ዋና መቀመጫውን ቻይና በማድረግ ከፈረንጆቹ 1950ዎቹ ጀምሮ በማምረት ላይ ይገኛል። ድርጅቱ በ2021 3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን ለዓለም በመሸጥ ቀዳሚ የዓለማችን ኩባንያ እንደሆነ ተገልጿል። ይህ የቻይና ኩባንያ ከኢትዮጵያው ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ ጋር አብሮ መስራቱን የገለጸ ሲሆን እስከ 20 ቶን እቃ የመጫን አቅም ያላቸው ተሽኩርካሪዎችን ለኢትዮጵያ ገበያ ማቅረቡን አስታውቋል። ኢኳቶሪያል ቢዝነስ ግሩፕ የተሽከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች…
Read More
የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርጉ መሆኑን ገለጹ

የሩሲያ መኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ሊያደርጉ መሆኑን ገለጹ

የሩሲያ  የመኪና አምራች ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ሲሆኑ በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጠና ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡ ከሩሲያ የላዳ እና ጋዝ ግሩፕ መኪና አምራች ኩባንያዎች የመጡ ተወካዮች ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ሰለሞን ጋር ተወያይተዋል፡፡ ለተወካዮቹ  በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ያለውን ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታ፣ ስለዘርፉ ማበረታቻዎች እንዲሁም በአፍሪካ ግንባር ቀደም ስለሆነው የድሬዳዋ የነጻ ንግድ ቀጠና አጠቃላይ ገለጻ ተደረገላቸዋል፡፡ የመኪና አምራች ኩባንያ ኃላፊዎቹ ከድሬዳዋ በተጨማሪ የቦሌ ለሚ እና ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን የስራ እንቅስቃሴና የምርት ሂደት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ኩባንያዎቹ በአውሮፓ፣ በደቡብ አሜሪካና የአፍሪካ ገበያዎች ለጤና ተቋማት፣ ለፀጥታ አካላት፣ ለጭነት አገልግሎት እንዲሁም ለግልና ለህዝብ ትራንስፖርት ዘርፍ…
Read More