EV

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ መኪኖች አዲስ መመሪያ አዘጋጀች

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል መሙያ ማሽን (ቻርጀር) መትከል የሚፈቅድ መመሪያ ጸደቀ መመሪያው በመንገዶች ግራና ቀኝ በየ50 ኪሎሜትር ልዩነት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መሙላት የሚችል ፈጣን ቻርጀር ጣቢያ ማቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ይሁንና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሃይል ማቅረብ የሚፈልጉ ተቋማት ከነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን ፈቃድ በመውሰድ እንዳለባቸው መመሪያ ይገልጻል። በተለያዩ ተቋማት የሚተከሉ የኤሌክትሪክ ሃይል መሙያዎች ከባለስልጣኑ ፈቃድ ማግኘት እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል፡፡ ነገር ግን በግል በቤት ውስጥ ከሚተከሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል መሙሊያ ማሽኖች ፈቃድ መጠየቅ የማይጠበቅባቸው መሆኑን ያመላከተው የተቋሙ መረጃ ከዚህ ውጭ ግን ማናቸውም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሃይል ሙሌት የሚሰጡ ማሽኖች መትከል የሚቻለው ከባለስልጣኑ ፈቃድ ሲያገኝ ብቻ መሆኑንም አመላክቷል። መመሪያው ለህዝብ በሽያጭ የኤሌክትሪክ ሃይል ሙሊት አገልግሎት የሚሰጡ ታሪፋቸው በባለስልጣኑ ሲጸድቅላቸው…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ከወራት ማመንታት በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ እገዳ መጣሉ ተገልጿል፡፡ መኪኖችን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ስራ የተሰማሩ ኩባንያዎች እንዳሉት ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማስገባት እንደማይችሉ እንደተነገራቸው ተናግረዋል። ከመካከለኛው ምስራቅ፣ ከአውሮፓና ደቡብ አፍሪቃ ያጓጓዟቸውን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ማስገባት እንደማይችሉ ከሶስት ሳምንት በፊት ተነግሯቸዋል። በእገዳው ሳቢያ ከፍተኛ መጉላላትና ኪሳራ እንደደረሰባቸው ባለጉዳዮቹ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል። ከሳምንታት በፊት የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማገዱን ለፓርላማ አባላት ሲያስታውቅ የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ እገዳው ተገባራዊ እንደማይደረግና በዕቅድ ደረጃ ያለ መሆኑን ተናግሮ ነበር። ይሁንና ባለፉት ቀናት የተለየ ፍላጎት ላላቸው የልማት ፕሮጀክቶችና ለህዝብ ትራንስፖርት የሚውሉ ካልሆኑ በቀር በነዳጅ የሚሰሩ…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ ልትከለክል መሆኗን ገለጸች

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር የስድስት ወራት ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ ሚኒስትሩ አቶ አለሙ ስሜ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ የሚደረገው ክልከላ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሩ አቶ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ለፓርላማው እንደተናገሩት፥ ነዳጅ የሚወስዱ ተሽከርካሪዎችን ለግል ጥቅማጥቅ ሆነ ለሌላ አላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የሚደረገውን እገዳ በጥብቅ እንደሚያስፈጽሙ ገልጸዋል። ውሳኔው ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር ተያይዞ ለሚነሱ ስጋቶች እና ከባህላዊ የነዳጅ ፍጆታ ጋር ተያይዞ እየጨመረ ለሚመጣው ወጭ ስልታዊ ምላሽ ነውም ተብሏል። እየጨመረ የመጣው የነዳጅ ወጪ ፖሊሲ አውጪዎች አገሪቱ በተለመዱት ተሽከርካሪዎች ላይ ያላትን ጥገኝነት እንዲገመግሙ እና የካርበን በካይ ጋዝ መጠንን ለመቀነስ ከሚደረገው…
Read More
ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

ኢትዮጵያ ቮልስዋገን የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ አገደች

በቻይና የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ ማገዷን አስታውቃለች፡፡ በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጵያ እየገባ የሚገኘው ቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ሕጋዊ የሆነ ፈቃድ አለመኖሩን የጀርመኑ ኩባንያ በኤንባሲው በኩል በደብዳቤ ለሚኒስቴሩ ማሳወቁ ተገልጿል፡፡ በመሆኑም በቻይና ሀገር የሚመረተው የቮልስ ዋገን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ሕጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስከሚረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ ታግዷል፡፡ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ ክትትል በማድረግና የሕጋዊነት ማረጋገጫ መረጃዎችን የማጥራት ስራም በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሠራ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ መንግስት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት እንዲመረቱ፣ እንዲገጣጠሙና ወደ ሀገር…
Read More