ኢኮኖሚ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 26 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግ እና ኤርባስ ጋር ድርድር ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 26 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግ እና ኤርባስ ጋር ድርድር ጀመረ

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ካዘዛቸው 26 አውሮፕላኖች ውስጥ ስምንቱን በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚረከብ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ገልጸዋል። ዋና ሥራ አስፈጻሚው አየር መንገዱ ተጨማሪ 26 አዳዲስ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ከቦይንግና ከኤርባስ ከተሰኙ ግዙፍ የአውሮፕላን አምራች ኩባንያዎች ድርድር በማድረግ ላይ እንደሆነ ጠቁመዋል። አየር መንገድ በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ስምንት አውሮፕላኖችን እንደሚረከብ አስታውቋል። ከተገዙት አውሮፕላኖች መካከል አየር መንገዱ ስምንት የመንገደኛ አውሮፕላኖች በጥቂት ወራት ውስጥ እንደሚረከብም ነው የገለጹት። ቀሪዎቹ የመንገደኞች አውሮፕላኖች በቀጣይ ጊዜያት እንደሚገቡ ገልጸው፤ አየር መንገዱ ሌሎች ተጨማሪ አውሮፕላኖችን ለማስገባት እቅድ እንዳለው ተናግረዋል። ጎን ለጎንም አየር መንገዱ በሰኔ ወር ከቦይንግ ኩባንያ ሊረከባቸው ግዥ የፈጸመባቸው ኹለት አውሮፕላኖችም በመጪው መስከረምና ጥቅምት ወራት እንደሚገቡ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ በረራውን ሰረዘ

አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገጾቹ ባሰራጨው መረጃ ወደ ደሴ፣ ጎንደር፣ እና ላሊበላ የሚያደርገውን በረራ ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ የተሰረዙት በረራዎች ነገ እና ከነገ በስቲያ ሊያደርጋቸው የነበሩ በረራዎች እንደሆኑ ገልጾ አየር መንገዱ ወደ ተጠቀሱት አካባቢዎች ለመጓዝ ትኬት የቆረጡ ደንበኞች በረራዎቹ እንደተመለሱ አስተናግዳለሁም ብሏል፡፡ ይሁንና አየር መንገዱ በምን በረራዎቹን እንደሰረዘ ያልገለጸ ሲሆን በአማራ ክልል እየተካሄዱ ባለው ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በአማራ ክልል በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጁ ይታወሳል፡፡ በአማራ ክልል ያጋጠመውን የፀጥታ መደፍረስ በመደበኛ የህግ ማስከበር ስርአት ለመቆጣጠር አዳጋች ሆኖ በመገኘቱ የፌደራል መንግስት አስፈላጊውን የህግ ማዕቀፍ እንዲተገብር የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መጠየቁ ይታወሳል። በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች…
Read More
በአማራ ክልል የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል የኢንተርኔት አገልግሎት ተቋረጠ

በአማራ ክልል በርካታ ከተሞች በሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ውጊያ እየተካሄደ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ በሁለቱ አካላት መካከል ውጊያ መጀመሩን ተከትሎ በአማራ ክልል የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ከነዋሪዎች አረጋግጠናል፡፡ በክልሉ ኢንተርኔት ለምን እንደተቋረጠ ኢትዮ ቴሌኮምም ሆነ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እስካሁን ያሉት ነገር የለም፡፡ ኢትዮጵያ ከሰሞኑ በቴሌግራም ላይ እገዳ የጣለች ሲሆን መተግበሪያው በቪፒኤን በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለው ጦርነት መባባሱን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ላሊበላ እና ጎንደር የሚያደርጋቸውን በረራዎች መሰረዙ ይታወሳል፡፡ የስፔን፣ ፖላንድ እና በርካታ ሀገራት ኢምባሲዎች ዜጎቻቸው ወደ አማራ ክልል እንዳይጓዙ በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡ ከወራት በፊት በኦሮሚያ ክልል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጋጥሟት የነበረዉን የመከፋፈል ድርጊትና የጳጳሳት ሹመነትን…
Read More
የአፍሪካ ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያና 84 ሚሊየን ዶላር ሰጠ

የአፍሪካ ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያና 84 ሚሊየን ዶላር ሰጠ

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ልማት ፈንድ ለስንዴ ምርትና ምርታማነት ማሻሻያ የሚውል የ84 ነጥብ ሶስት  ሚሊየን ዶላር (4. 5 ቢሊየን ብር) የልማት ድጋፍ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ ከልማት ደጋፋ ውስጥ 54 ሚሊየን ዶላር ከአፍሪካ ልማት ፈንድ፣ 20 ሚሊየን ዶላር ከኔዘርላንድ መንግሰት፣ እንዲሁም 10 ነጥብ ሶስት ሚሊየን ዶላር ደግሞ ሌሎች ድርጅቶች ሰጥተዋል። የልማት ድጋፋ በአነስተኛ እርሻ የስንዴ አምራች ገበሬዎችን ምርትና ምርታማነትን ለማሻሻል የሚውል ሲሆን ይህን ዕውን ለማድረግ እንዲቻል ድጋፉ ከአካባቢ ጋር ተስማሚ የስንዴ ምርት ለማምረት ፣ የገበያ መሰረተ ልማቶችንና ትስስርን ለማሳደግ እንዲሁም በዘርፋ ያሉ ፕሮጀክቶችን ለማስተዳደር የሚውል ነው፡፡ የልማት ድጋፋን ስምምነት በኢትዮጵያ መንግስትን በኩል የገንዘብ ሚነስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ፈንድን በመወከል ዶ/ር አብዱል…
Read More
ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ኢትዮጵያ ለአደይ አበባ ስታድየም አዲስ የግንባታ ጨረታ ልታወጣ ነው

ለረዥም ጊዜ ተቋርጦ የቆየውን የአደይ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ በአዲሱ በጀት ዓመት እንደገና ለማስጀመር በጀት መያዙን ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ገልጿል ። የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በ48 ሄክታር መሬት ላይ የሚገነባውና 62ሺ ተመልካች የመያዝ አቅም ያለው ብሔራዊ ስታዲየም ግንባታን ለማስቀጠል በ2016 ዓ.ም በጀት የተያዘለት በመሆኑ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ጨረታ ወጥቶ ግንባታው ይጀመራል። የብሔራዊ ስታዲየሙ ግንባታ በቻይናው ኩባንያ ይካሄድ እንደነበረ አስታውሰው፤ ግንባታው በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ መቆየቱን ገልፀዋል። በኋላም የግንባታ ተቋራጩ ለሥራው ያቀረበው የዋጋ ማስተካከያ ከገበያ በላይ የተጋነነ በመሆኑ መንግሥት ከያዘው በጀት ጋር ሊመጣጠን አልቻለም። በዚህም ከግንባታ ተቋራጩ ጋር ያለው ውል እንዲቋረጥ መደረጉን ሚኒስትሩ ተናግረዋል።…
Read More
ሩሲያ ለአፍሪካ ገበያ በግብጽ የላዳ መኪና ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

ሩሲያ ለአፍሪካ ገበያ በግብጽ የላዳ መኪና ፋብሪካ ልትገነባ መሆኗን ገለጸች

የሩሲያ ምርት የሆነው ላዳ መኪና በኢትዮጵያ እና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ተመራጭ ነበሩ። ለዓመታት ገበያውን ተቆጣጥረውት የቆዩት የሩሲያ ላዳ መኪኖች ቀስ በቀስ ከዓለም እና አፍሪካ ገበያዎች እየጠፉ መጥተዋል። ኩባንያው ምርቶቹን ወደ አፍሪካ ገበያዎች ማቅረብ ያቆመው ከቀዝቃዛው ጦርነት ጋር በተያያዘ የሩሲያ ተጽዕኖ እየቀነሰ በመምጣቱ እና በገበያ ውድድር ምክንያት እንደሆነ ድርጅቱ ገልጿል። ሩሲያ ወደ አፍሪካ ገበያዎች ዳግም የመመለስ ፍላጎት ማሳየቷን ተከትሎ ኩባንያው ከወራት በፊት በኢትዮጵያ እና ሌሎች የአፍሪካ ከተሞች ምቹ ሁኔታዎችን ተመልክቶ ተመልሷል። የኩባንያው ሀላፊዎች በኢትዮጵያ በነበራቸው ቆይታ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ሀላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገውም ነበር። ይሁንና በፒተርስግበርግ ከየማ እየተካሄደ ባለው የሩሲያ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ መካሄዱን ተከትሎ ኩባንያው ዋና ሙቀመጫውን ግብጽ ለማድረግ መወሰኑን…
Read More
ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ከቡና የምታገኘው ገቢ የ90 ሚሊዮን ዶላር ቅናሽ አሳየ

ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት ከተላከ ቡና 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝታለች። ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው የቡና ምርት መጠን ከዓመት ዓመት ማሽቆልቆሉን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር ገልጿል፡፡ የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ግዛት ወርቁ ኢትዮጵያ በ2014 ዓ. ም ለዓለም ገበያ ያቀረበችው የቡና መጠን 302 ሺሕ ቶን ነበር። በዘንድሮው ማለትም በ2015 ዓመት ግን 240 ሺሕ ቶን ብቻ ቡና ለዓለም ገበያ ማቅረቧን የኢትዮጵያ ቡና ላኪዎች ማህበር አስታውቋል። ወደ ውጪ ሀገራት የተላከው ቡና ከባለፈው ዓመት ለዓለም ገበያ ከቀረበው የቡና ምርት ጋር ሲንጻጸር በ62 ሺሕ ቶን ቅናሽ አሳይቷል ተብላል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም፤ ኢትዮጵያ በዘንድሮው ዓመት ለዓለም ገበያ ካቀረበችው ቡና 1 ነጥብ 33 ቢሊዮን ዶላር…
Read More
ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ 400 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ

ዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ 400 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አደረገ

ኢትዮጵያና የአለም ባንክ ለሰው ሀብት ልማት አገልግሎት የሚውል የ400 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ስምምነት በበይነ መረብ በተካሄደ ሥነ-ስርዓት ተፈራርመዋል፡፡ በስምምነቱ ከተፈረመው 400 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 350 ሚሊዮን ዶላር የልማት ድጋፍ ሲሆን 50 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ብድር መሆኑ ታውቋል፡፡ የፋይናንስ ድጋፉ ለሰው ሀብት ልማት ማለትም የትምህርትን ጥራትንና ውጤታማነትን ለማሻሻልና የስርዓተ ምግብን አገልግሎት ለማጎልበት የሚውል ሲሆን፤ ከአገልግሎቱም በመላ አገሪቱ የሚገኙ ልጃገረዶችና ታዳጊ ወጣቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ የሰው ሀብት ልማት አገልግሎቱ በግጭትና ድርቅ የተጎዱ አካባቢዎችን የሚያካትት ሲሆን፤ የማህበራዊ አገልግሎቶች አሰጣጥን ለማጠናከርና ተጠያቂነትን ለማስፈንም አስተዋጽዖ እንዳለው ተነግሯል፡፡ የፋይናንስ ድጋፉ ውጤታማ የመማር ማስተማር ሂደትን ለማረጋጋጥ የሚያግዝ ከመሆኑም በላይ በተመረጡ ወረዳዎች የስርዓተ ምግብ አገልግሎትን…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 90 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቀደ

ኢትዮ ቴሌኮም በ2016 በጀት ዓመት 90 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቀደ

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ የተቋሙን የ2016 በጀት ዓመት እቅድን ይፋ አድርገዋል። ስራ አስፈጻሚዋ በዚህ ጊዜ እንዳሉት በተያዘው በጀት ዓመት ከአጠቃላይ የቴሌኮም አገልግሎቶች 90 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል። ድርጅቱ በ2016 በጀት ዓመት 13 ሚሊዮን አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት የተቋሙን አጠቃላይ ደንበኞች ቁጥር ወደ 92 ሚሊዮን የማድረስ ውጥን መያዙንም ሀላፊዋ አክለዋል። የቴሌብር ደንበኞችን ወደ 44 ነጥብ 1 ሚሊዮን፣ የሞባይል ድምጽ አገልግሎት ተጠቃሚዎችን ቁጥር 75 ሚሊዮን እንዲሁን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎችን ወደ 41 ሚሊዮን ማድረስም የተቋሙ ሌላኛው ግብ ነው ተብሏል። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎቶች የመጠቀም ምጣኔን ወደ 71 በመቶ ለማድረስ መታቀዱን ወይዘሪት ፍሬህይወት ገልጸዋል። የቴሌኮም መሰረተ ልማቶችን ከማስፋፋት…
Read More
በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

በአዲስ አበባ 100 ሺህ ቤቶችን በአንድ ዓመት ውስጥ ለመገንባት ስምምነት ተፈረመ

የቤቶቹ ግንባታ በ68 የሪል ኢስቴት አልሚዎች እንደሚገነባ የተገለጸ ሲሆን መንግሥት መሬት በነጻ ለማቅረብ ተስማምቷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመንግሥትና በግል አጋርነት ፕሮጀክት አማካይነት በመረጣቸው ሪል ስቴት አልሚዎች፣ ከግማሽ ትሪሊዮን ብር በላይ ወጪ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ሊካሄድ ነው ተብሏል። በዚህ ፕሮግራም ሥር እንዲሳተፉ 68 ሪል ስቴት አልሚዎችን የመረጠ ሲሆን፤ አልሚዎቹም በተቀመጠው 70/30 አጋርነት መሠረት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተጣምረው ግንባታውን ለማካሄድ ውል መግባታቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ከእነዚህም አልሚዎች ውስጥ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ ኦቪድ ግሩፕ፣ ፍሊንትስቶን ሆምስ፣ እንይ ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ሪል ስቴትና ሌሎችም ይገኙበታል። የከተማ አስተዳደሩ የቤቶቹን ግንባታ ለማካሄድ የሚያስፈልገውን መሬት ከሊዝ ነፃ ማቅረብና መሠረተ ልማቶችን የማሟላት ኃላፊነት አለበት ተብሏል። የሪል ስቴድ ድርጅቶች…
Read More