ኢኮኖሚ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከያዝነው ዓመት የካቲት ወር ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ባሉት አምስት ወራት በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ገደብ ጥላለች። ኢትዮጵያ የኢንተርኔት እገዳውን የጣለችው በቲክቶክ፣ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ዩቲዩብ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ነው። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት የሌለው ነው ሲልም ገልጿል፡፡ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጥ ትኩረት ሊያገኝ ባለመቻሉም የሰብዓዊ መብቶች እሴቶችን እንዲሁም በሕገ መንግሥቱ የተጠበቁ…
Read More
በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በከተማዋ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከ4 ሺህ በላይ ትዳር መፍረሱ ተገልጿል የፈረሰው ትዳር ቁጥር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር በ60 በመቶ ጨምሯል ተብሏል በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት 4 ሺህ 696 ትዳር በፍቺ መጠናቀቁ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ እንደገለፁት በ2015 ዓ.ም ከማዕከል እስከ ወረዳ ለ2 ሚሊየን 239 ሺህ 713 ተገልጋዮች አገልግሎት ተሰጥቷል። ከዚህ ውስጥ 37 ሺህ 397 ጋብቻ እና 4 ሺህ 696 ፍቺ መሆኑን ተናግረዋል። ዘንድሮ የተመዘገበው የፍቺ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር፥ የ60 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል። ለአብነትም በ2014 ዓ.ም 2 ሺህ 937 ፍቺ መመዝገቡን እና በ2015 ዓ.ም ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ግብጽ በሱዳን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት የጎረቤት ሀገራት መሪዎችን መጋበዟ ይታወሳል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የሱዳን ጎረቤት ሀገራት በመድረኩ ላይ ለመሳተፍ ወደ ካይሮ ያመሩ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከውይይቱ በተጓዳኝ ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መወያየታቸው ተገልጿል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ደግሞ የመሪዎቹ ዋነኛ መወያያ እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ግብጽን እና ሱዳንን የመጉዳት ፍላጎት የላትም የተባለ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ ስለመስማማታቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳንም በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለባቸውን አለመግባባት በአራት ወራት ውስጥ በሚያደርጉት ውይይት ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት የመንጃ ፍቃድ ስልጠና መስጠት ተጀመረ አሁን ላይ 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል ተብሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር ጀኔራል ዳመና ዳሮታ እንዳሉት ለመጀመሪያ ጊዜ በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለታራሚዎች የአሽከርካሪ መንጃ ፍቃድ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ስልጠናው በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ታሪክ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል የመጀመሪያው ሲሆን ታራሚዎች የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በቀጥታ ወደ ስራ አለም እንዲገቡ የሚያግዝ ነው ተብሏል። ለመጀመሪያ ጊዜ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል ሲከፍት ለታራሚው እና ለፖሊስ አባላት እንዲያገለግል ታስቦ ሲሆን እስካሁን 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል። የህግ ታራሚዎችን በይበልጥ የሙያ ባለቤት የማድረግ ስራ በቀጣይ በማስፋፋት ከመንጃ ፍቃድ በተጨማሪ የመካኒክነት ስልጠናና የተሽከርካሪ…
Read More
በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በሸገር ከተማ አስተዳደር በሚገኘው ኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ለባለእድለኞች በተላለፉ ቤቶች ውስጥ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው በመግባት ወረራ እየፈጸሙ መሆኑን የኮንዶሚኒየሙ ሕጋዊ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በኮንዶሚኒየሙ የእጣ እድለኞች ሆነው ለባለቤቶች ቁልፍ ተላለፈው፤ ነገር ግን ተቆልፈው በተቀመጡ ቤቶች እና እስካሁን ለባለእድለኞች ባልተላለፉ ቤቶች ላይ የማይታወቁ ሰዎች ወረራ እየፈጸሙ ነው ተብሏል። ይህን ድርጊት ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ የኮንዶሚኒየም የጥበቃ ሠራተኞች ላይም ዛቻ እና ማስፈራሪያ በማድረስ ሰዎቹ በኃይል እየገቡ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡ ነዋሪዎቹ አክለውም፤ “ተዘግቶ የተቀመጠን ቤት በኃይል ሰብረው ገብተው ወረራ ሲፈጽሙ አንድም የመንግሥት አካል ሊያሰቆማቸው የሞከረ የለም፡፡” ሲሉ ተደምጠዋል። ከመጋቢት 2015 ጀመሮ በኮንዶሚኒየሞቹ ላይ ከፍተኛ ወረራ እየተካሄደ መሆኑን በመጠቆምም፤ “ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል በተደጋጋሚ…
Read More
ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ዋና መቀመጫውን ቻይና ያደረገው ቴክኖ ሞባይል አዲስ የሞባይል ምርቱን ለኢትዮጵያ ደንበኞቹ በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል። ቴክኖ ሞባይል ይፋ ያደረገው ካሞን 20 አዲስ ምርት የአምስተኛ ትውልድ ወይም 5G ኔትወርክ አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል። እንዲሁም ይህ አዲስ ስልክ 8 ጌጋ ባይት ራም እና 256 ጌጋ ባይት መጠን ያላቸው መረጃዎችን የመያዝ አቅም ሲኖረው ለተክም ሰዓት ማስጠቀም የሚያስችል ባትሪም አለው ተብሏል። ሶስት ካሜራ እንዳለው የተገለጸው ይህ አዲስ የቴክኖ ሞባይል ስልክ ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ ለደንበኞቹ ቀርቧል። ቴክኖ ሞባይል በትራንሽን ኩባንያ ስር ሆኖ በፈረንጆቹ 2006 ላይ የተመሰረተ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው። በጆርጁ ዙ የተቋቋመው ቴክኖ ሞባይል ዋና መቀመጫውን በቻይናዋ ሸንዘን አድርጎ በመላው ዓለም ምርቶቹን ለደንበኞቹ በማቅረብ…
Read More
ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስከ መስከረም ውሀ እንደማይዝ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ተናግረዋል። ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ እየሰጡ ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ከአባላቱ ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ውሀ ሙሌት አይከናወንም ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሱዳንን እና ግብፅ ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ሙሌቱ እስከ መስከረም መጀመሪያ አታከናውንም" ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናግረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሀምሌ ወር ጀምር ውሀ ሲይዝ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ ግን ውሀ የመያዣው ጊዜ ወደ መስከረም መዛወሩ ተገልጿል። እንደ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለጻ የዘንድሮው ውሀ ሙሌት ወደ ግብጽ እና ሱዳን በቂ የዉሃ ከደረሰ በኋላ ሙሌቱ…
Read More
ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ዘላቂ ዲሞክራሲን ለማስፈን የሚያስችላትን የምርጫ ስርአት እንድታጠናክር ለማግዝ የሚውል የ30 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የፋናንስ ድጋፍ ስምምነት ፈርማለች፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት መካካል ተፈርሟል፡፡ የበጀት ድጋፉ የምርጫ ቦርድ ተቋማዊ መዋቅርን ለማጠናከር ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ አሳታፊ ፣ተአማኒና ደረጃውን የጠበቀ ምርጫና ህዝበ ውሳኔ እንዲያካሂድ ተቋሙን ማጠናከር፣ ከሲቪክ ተቋማት በጋራ በመሆን በምርጫ ሂደት የሴቶችና ወጣቶች ተሳትፎን ለማሳደግ ይውላል ተብሏል፡፡ እንዲሁም የበጀት ድጋፉ በኢትዮጵያ ነፃ ፍትሀዊ እና ተአማኒ ምርጫ እንዲያከሂድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንደሚውልም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ይህ የበጀት ድጋፍ ፕሮጀክት በሚቀጥሉት አራት አመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን የሀገሪቱን የምርጫ ስርአት በማጠናከር ዘላቂ ዴሞክራሲን ለማስፈን አስተዋጽኦ…
Read More
ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

በኢትዮጵያ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት በስፋት ጥቅም ላይ ከዋለ የአገር ዉስጥ እድገት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጨምር ዓለም አቀፍ የሞባይል ግንኙነት ስርዓት ማኅበር አስታውቋል። ይህም የሚሆነው በፈረንጆች 2030 ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ 60 በመቶ ያህሉ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ከሆኑ ነው ያለው ማኅበሩ፤ በተጨማሪም 700 ሺሕ ሰዎችን ከአስከፊ ድህነት እንደሚያወጣና የታክስ ገቢን በ300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምር አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በአንፃራዊነት 99 በመቶ የኔትወርክ ሽፋን ተደራሽነት ቢኖርም፤ የኔትዎርክ ጥራት አስተማማኝ አለመሆን፣ የዲጂታል ስርዓቱ ግንዛቤ ጉድለት፣ የዕምነትና የመረጃ ግላዊነትና ደህንነት ጥያቄ እንዲሁም የግብይቶች በተደጋጋሚ መስተጓጎል የሞባይል ገንዘብ ክፍያን እና አጠቃቀም ላይ እንቅፋት እየሆነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በ2021 የኤሌክትሪክ ኃይል ያላቸው ኢትዮጵያውያን 51…
Read More
አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ የታዋቂውን ሩሲያዊ ደራሲ ፑሽኪን ሐውልትን ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች የሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በፈረንጆቹ 2002 ላይ ነበር የታዋቂውን የሩሲያዊ የስነ ጽሁፍ ሰው አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሀውልት በስጦታ መልኩ ለአዲስ አበባ የሰጠችው። ይህ ሀውልት ለረጅም ዓመታት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ስር ባለ አንድ አደባባይን የፑሽኪን አደባባይ በሚል የሰየመችው። በዚህ አደባባይ ላይም የፑሽኪን ሐውልት ተተክሎ የቆየ ቢሆንም የትራፊክ መጨናነቅን ለማስቀረት በሚል አደባባዩ ፈርሷል። የአሌክሳንደር ፑሽኪን ሀውልትም ወደ ኢትዮጵያ ሙዚየም ግቢ ውስጥ እንዲቀመጥ ተደርጎ ቆይቷል። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ለአልዐይን እንዳሉት የፑሽኪን ሀውልት ወደ አደባባይ ወጥቶ ይተከላል ብለዋል። "ሀውልቱ የሩሲያን እና ኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ክብር…
Read More