Addisababapolice

አዲስ አበባ የጦር መሳሪያ በታጠቁ ድሮኖች ትጠበቃለች ተባለ

አዲስ አበባ የጦር መሳሪያ በታጠቁ ድሮኖች ትጠበቃለች ተባለ

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በአዲ አበባ የታጠቁ ድሮኖችን ለጸጥታ ስራ እንደሚጠቀም አስታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ አስተዳደር የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና ትራፊክ ፍሰት ለመቆጣጠር ይሰማራሉ የተባሉ ድሮኖች ቁጥጥር ብቻ ሳይሆን እርምጃም እንደሚወስዱ አስታውቋል። የትራፊክ ፍሰት እና በበዓላት ወቅት የከተማዋን ጸጥታ ለመቆጣጠር በርካታ ድሮኖች መግባታቸው እና የሚቆጣጠሯቸው ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ስልጠና አጠናቅቀው በቀጣይ ጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ ስራ እንደሚገቡ ተገልጿል፡፡ ድሮኖቹ የከተማዋን ፀጥታ ሁኔታና የትራፊክ ፍሰት ከመቆጣጠር ባሻገር እርምጃም እንደሚወስዱ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ተናግሯል፡፡ በቅርብ ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ፍሰትና አጠቃላይ የፀጥታ ሁኔታ እንዲሁም ታላላቅ ፕሮግራሞችን ቁጥጥር ማድረግ የሚችሉ የድሮኖች ስምሪት እንደሚደረግ፣ የፀጥታ ጥምር ግብረ ኃይል ከቀናት በፊት መግለጹ ይታወቃል፡፡ አሁን ላይ በርካታ ድሮኖች…
Read More
በአዲስ አበባ በእስረኛ ምግብ ውስጥ ካናቢስ የተሰኘው አደገኛ ዕጽ ተያዘ

በአዲስ አበባ በእስረኛ ምግብ ውስጥ ካናቢስ የተሰኘው አደገኛ ዕጽ ተያዘ

በምግብ ውስጥ  አደንዛዥ ዕፅ  ደብቆ ተጠርጣሪ ለመጠየቅ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የሄደው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል። ግለሰቡ ከናቢስ የተባለውን አደንዛዥ ዕፅ ይዞ በወንጀል ተጠርጥሮ የታሰረ ጓደኛውን ለመጠየቅ የሄደው ወደ ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ነበር፡፡ ከክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በወንጀል ተጠርጥሮ የታሰረ ጓደኛውን ለመጠየቅ ምግብ ይዞለት የሄደው ይኸው ተጠርጣሪ ከድፍረትም ድፍረት የሚያሰኝ ተግባር ነበር የፈፀመው፡፡ በወቅቱ በሳህን የተቋጠረው ምግብ እንጀራ ፍርፍር በማካሮኒ ነበር፡፡  በእነዚያ የማካሮኒ ቀዳዳዎች ውስጥ የሚያብለጨልጩ ነገሮች ተወታትፈዋል፡፡ ምግቡን ፈትሸው የሚያስገቡት የፖሊስ አባላት ባዩት ነገር ተጠራጥረዋል፤ ምግቡ ተዘርግፎ ሲፈተሽ ብዛት 51 የማካሮኒ ፍሬዎች በተጠቀለሉ የአልሙኒየም ወረቀቶች  አባብጠዋል፡፡ ወረቀቶቹን በመፍታት ለማየት ሲሞከርም ካናቢስ የተባለው አደንዛዥ ዕፅ ሆኖ…
Read More
በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

በአዲስ አበባ ግብረሰዶም ይፈምባቸዋል የተባሉ መዝናኛ ቤቶች ታሸጉ

አዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በከተማዋ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚፈጸምባቸው ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ፖሊስ እርምጃውን እየወሰደባቸው ያሉት ሆቴሎች፣ ባሮችና ሬስቶራንቶች ሲሆኑ ከአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር እንደሆነ ገልጿል። የተመሳሳይ ጾታ መዝናና ቤቶች ከነባሩ የሀገሪቷ ባህል፣ ወግ፣ የአኗኗር ስርዓት እና ኃይማኖቶች ባፈነገጠ መልኩ ወንጀሎች ይፈጸምባቸው ነበርም ተብላል። ፖሊስ የግብረ-ሰዶም ተግባር በሚያስፈጽሙ ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ፔንሲዮኖችና መሰል የመዝናኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ከህብረተሰቡ ጥቆማ እንደደረሰውም አስታውቋል ። የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የግብረ-ሰዶም ተግባር መፈጸምና ማስፈጸም በኢትዮጵያ በሥራ ላይ ባሉ ሕጎች የተከለከለ ናቸው ብሏል። ፖሊስ የተመሳሳይ ጾታ መዝናኛ ቤቶች ባለቤቶች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየታጣራባቸው እንደሆነም አስታውቋል።
Read More
በቀን 35 ሺህ ብር ይቆጥቡ የነበሩ የሿሿ ሌቦች ተያዙ

በቀን 35 ሺህ ብር ይቆጥቡ የነበሩ የሿሿ ሌቦች ተያዙ

በአዲስ አበባ የ"ሿሿ " ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች በተለምዶ "ሿሿ "የሚባለውን ወንጀል ሲፈፅሙ የነበሩ 25 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል። ወንጀል ፈፃሚዎቹ ኃይል በመጠቀም ሚያዚያ 23 ቀን 2015 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አንበሳ ጋራዥ አካባቢ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 ኦሮ 86853 ነጭ ሚኒባስ በመጠቀም ከአንድ ግለሰብ ላይ 10ሺ ብርና ግምቱ 14 ሺብር የሚያወጣ ሞባይል ስልክ ሰርቀው ይሰወራሉ፡፡ ፖሊስ ጠንካራ  ክትትል  በማድረግ ወንጀል ፈፃሚዎቹን ከነተሽከርካሪው በቁጥጥር ስር በማዋልና ምርመራ በማስፋት ተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የሚፈፅሙ 14 ወንጀል ፈፃሚዎችንና  የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 ኦሮ 79184 ሚኒባስ ተሽከርካሪን…
Read More
በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሯቸው ውስጥ በአዲስ አበባ ፖሊስ አባል ተገደሉ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር የሆነ አባል ነው፡፡ የፖሊስ አባሉ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት ያመለከተውን ማመልከቻ ለመከታተል ወደ ወረዳው መጽህፈት ቤት መሄዱን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ የወረዳው ስራ አስፈጻሚም ጉዳዩን ተመልክቶ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ በሚል ምክንያት ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ መግደሉን…
Read More
በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ። በዘንድሮው የአድዋ በኣል በአዲስ አበባ ምኒልክ አደባባይ የጸጥታ ሀይሎች በዜጎች ላይ ያልተገባ ድርጊት መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እና ሌሎችም ተቋማት መናገራቸው ይታቀሳል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዪ ዙሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዕለቱ የህግ ጥሰት በፈጸሙ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። ኮሚሽኑ አክሎም በዓሉ በተከበረበት እለት የከተማዋን ሰላም አውከዋል በሚል 878 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ብሏል። በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥም 557ቱ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን…
Read More