Murder

አባቱን በቤንዚል አቃጥሎ የገደለው ሰው በፖሊስ ተያዘ

አባቱን በቤንዚል አቃጥሎ የገደለው ሰው በፖሊስ ተያዘ

ፖሊስ በአዲስ አበባ ወላጅ አባቱን በቤንዚን አቃጥሎ የገደለን ተጠጣሪ መያዙን ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ቤተሰቦቼ ለእኔ ምንም ቦታ የላቸውም በሚል ምክንያት ወላጅ አባቱንና ታላቅ ወንድሙን ቤንዚል በመርጨት በቁም ያቃጠላቸው ተከሳሽ በቁጥጥር ማዋሉን ገልጿል። ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ክብረ ደመና ሙሉ ወንጌል አካባቢ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ነው ተብሏል። ተከሳሹ ከዚህ ቀደም በሌላ ወንጀል ተከሶ ታስሮ የነበረና በፍርድ ቤት ዋስትና የተለቀቀ እንደነበር የገለጸው ፖሊስ ከእናቴ በስተቀር ለእኔ የሚያስብልኝ የለም በሚል ምክንያት ወንጀሉን ለመፈጸም እንደተነሳሳም ተገልጿል። ከሳምንት በፊትም በአንድ ሺህ ስድስት መቶ ብር ቤንዚል በመግዛት አባቱና ታላቅ…
Read More
በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ

በአዲስ አበባ አንድ የወረዳ አመራር በፖሊስ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሯቸው ውስጥ በአዲስ አበባ ፖሊስ አባል ተገደሉ። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ግድያውን የፈፀመው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የካሳንቺስ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት የቀጠና ኦፊሰር የሆነ አባል ነው፡፡ የፖሊስ አባሉ የግል ጉዳዩ እንዲፈፀምለት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ጽ/ቤት ያመለከተውን ማመልከቻ ለመከታተል ወደ ወረዳው መጽህፈት ቤት መሄዱን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ የወረዳው ስራ አስፈጻሚም ጉዳዩን ተመልክቶ ምላሽ እንደሚሰጠው የተገለፀለት ቢሆንም ጥያቄዬ እንዳይፈፀም የከለከልከው አንተነህ በሚል ምክንያት ቢሯቸው ውስጥ በስራ ላይ እንዳሉ በታጠቀው ሽጉጥ መግደሉን…
Read More
በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ

በአዲስ አበባ የአንድ ወረዳ ስራ አስፈጻሚ ተገደሉ በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ አለባቸው አሞኜ በቢሮአቸው ውስጥ ተገደሉ። የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ ተገልጋይ በሽጉጥ ተገድለዋል። ክፍለ ከተማው ስለ ግድያው ተጨማሪ መረጃ ባያደርግም ግድያውን ፈጽማል የተባለለው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ብሏል። ክፍለከተማው ባወጣው መግለጫ " አቶ አለባቸው በስራ ቁርጠኝነት የሚታወቁ ናቸው" "በበርካታ መንግስታዊና ህዝባዊ ተግባራት አርዓያነት ያለው ስራ የሰሩና ያስተባበሩ አመራራችን ነበሩ " ሲል ገልጿል። አመራሩ በደረሰባቸው ጥቃት ወደ ህክምና ቦታ ቢወሰዱም ህይወታቸውን ማትረፍ እንዳልተቻለ ተገልጿል።
Read More
በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ

በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ

በወላይታ እናት ከጎረቤቷ ጋር ያላትን የፍቅር ግንኙነት ያወቀ ህጻን በመርዝ ተገደለ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ ወረዳ በአይጥ መርዝ የተመረዘ በሶ ለልጇ አጠጥታለች የተባለችዉ የ32 ዓመቷ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሏን ፖሊስ አስታወቀ። በዞኑ ሶዶ ዙሪያ ወረዳ ቶሚ ገረራ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችዉ ይህች ሴት ጎረቤቷ ከሆነ አባወራ ጋር በድብቅ የፍቅር ግንኙነት ጀምራለች በሚል የሚወራዉ ወሬ ከ16 አመቱ ታዳጊ ልጇ ጆሮ ይደርሳል። ልጅም እናቱ ከጎረቤታቸው ጋር የድብቅ ፍቅር ግንኙነት መመስረቷን ተከታትሎ ካረጋገጠ በኋላ በትህትና ሲያዋራት ጥፋቷን አምና ነበር ተብሏል። ይሁንና የድብቅ ፍቅር ግንኙነቷን ለባሏ እንዳይነግርባት ስጋት የገባት ይህች እናት ልጇን መርዝ አብልታ እንደገደለች ፖሊስ ገልጿል። እንደ ደቡብ ፖሊስ ምርመራ ከሆነ ይህች…
Read More