18
Aug
19ኛው የአፍሪካ አካባቢ ጥበቃ ሚንስትሮች ጉባኤ የአፍሪካን ችግሮች ለመፍታት እድሎችን መጠቀም እና ትብብርን ማጎልበት" በሚል ሀሳብ በአዲስ አቡባ ተካሂዷል። በዚህ ጉባኤ ላይ አፍሪካ አካባቢ ጥበቃ ሚንስትሮች፣ የዘንድሮው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዓመታዊ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አዘጋጅ ሀገር ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ሱልጣን አልጃቢር ተገኝተዋል። እንዲሁም የአካባቢ ጥበቃ ተቆርቋሪዎች፣ ተመራማሪዎች እና ተቋማት መሪዎች እንደተገኙ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር እና ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የአየር ንብረት ለውጥ የአፍሪካን የምግብ ዋስትና እየፈተነ ነው ብለዋል። አቶ ደመቀ አክለውም ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን ለመከላከል እና ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ አረንጓዴ አሻራ ስትራቴጂ ነድፋ እየተገበረች መሆኗንም ጠቅሰዋል። የኮፕ28 አለም አቀፍ አየር…