መነሻ ገፅ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከውጭ ጎብኚዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገለጸ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ከሀገር ውስጥ ጎብኚዎች 44 ቢሊዮን ብር አግኝታለች። እንዲሁም ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ደግሞ 2 ቢሊዮን ዶላር ማግኘቷ ተገልጿል ። የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በተያዘው በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ ኢትዮጵያ በ504,840 በሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ተጎብኝታለች። ከነዚህ ጎብኚዎችም ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷን ሚንስቴሩ ጠቅሷል። ቱሪስቶች፤ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶች የተገኙ ተሳታፊዎችና የቢዝነስ ሰዎችም በዚህ ሪፖርት ተካተዋል። በአዲስ አበባ የቱሪስት ቆይታም በአማካይ ከ5 እስከ 6 ቀናት እንደሆነም በሪፖርቱ ተጠቅሷል። ከሀገር ውስጥ ጎብኝዎችም 44 ቢሊዮን ብር መገኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ሚኒስቴሩ ካስቀመጠው 32.9 ቢሊዮን ብር እቅድ…
Read More
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የአሜሪካ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርትን ውድቅ አደረገች

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን በሚመለከት በአሜሪካ የወጣውን መግለጫ ውድቅ አደረገችየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ሁሉም ተሳታፊዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን አስታውቋል። ዋሽንግተን በኢትዮጵያ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል ሲል የደረሰችበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።  በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።  የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ…
Read More
ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች

ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች

ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪዋን በሞት አጣች ታዋቂው የአካባቢ ጉዳይ ሳይንስቲስት ዶክተር ተወልደ ብርሃን ገብረእግዚአብሄር በ 83 ዓመታቸው ህይወታቸው አልፋል። ዶ/ር ተወልደብርሃን በትግራይ ክልል በአድዋ ከተማ አቅራቢያ ባለችው ‹‹አዲ-ስላም›› የተሰኘች የገጠር መንደር  የተወለዱ ሲሆን ፣ በቀለም ትምህርት ገፍተው የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በ1955 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተቀበሉ በኋላ የሁለተኛ እና ዶክትሬት ዲግሪያቸውን ከዌልስ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡ በአካባቢ ጥበቃ ዘርፍ አገልግሎት የተከበረ ሥም ያላቸው ዶክተር ተወልደ በዘርፉ ላደረጉት ምርምርና በጉዳዩ ዙሪያ ከፍተኛ ግንዛቤ እንዲፈጠር ላደረጉት ጥረት በ2000 Right Livlihood Award ሽልማት አግኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በ2006 ዓመት የተባበሩት መንግሥታት በአካባቢ ጥበቃ ዙሪያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሰዎች የሚሰጠውን Champions of the Earth ሽልማት አግኝተዋል፡፡ የተማሩበት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ…
Read More
ዋሊያዎቹ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጉት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቀኑ

ዋሊያዎቹ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጉት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቀኑ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ለሚያደርገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቅንቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ከጊኒ ብሔራዊ ቡድን ጋር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታውን መጋቢት 15 እና 18 ቀን 2015 ዓ.ም በሞሮኮ ያደርጋል። የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ከመጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ልምምዳቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዋልያዎቹ ከትናንት በስቲያ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር ባደረጉት የአቋም መለኪያ ጨዋታ በከነዓን ማርክነህ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አራት ከግብጽ፣ ከማላዊና ከጊኒ ጋር ተደልድሏል፡፡ እስከአሁን…
Read More
የሎስ አንጀለስ ማራቶን በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቀቀ

የሎስ አንጀለስ ማራቶን በኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ የማራቶን ውድድሮችን አሸነፉ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ ሀገራት በተካሄዱ የማራቶን ውድድሮች ድል ማስመዝገብ ችለዋል። በቻይና ሸንዤን በተደረገ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያውያኑ ድል የቀናቸው ሲሆን፤በወንዶች አትሌት ባንታየሁ አዳነ በሴቶች አገሬ ታምር በአንደኝነት አጠናቀዋል። በአሜሪካ ሎሳንጀለስ በተካሄደ የወንዶች ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር ቀዳሚ መሆን ሲችል ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት የማነ ጸጋዬ ደግሞ ሁለተኛ ሆኖ ውድድሩን ጨርሷል። በባርሴሎና በተደረገ የማራቶን ውድድርም ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ዘይነባ ይመር ውድድሩን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ በአሜሪካ የኒዮርክ ግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ ደግሞ በሴቶች አትሌት ሰንበሬ ተፈሪ ሁለተኛ ሆና ውድድሯን አጠናቃለች። በታይዋን ታይፔ በተደረገው የሴቶች ማራቶን ውድድርም በቀለች ጉደታ፣ መሰረት ድንቄ እና ገበያነሽ አየለ ከአንድኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃን…
Read More
ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ ከጦርነት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ

ኢትዮጵያ በጦርነት ከደረሰባት ውድመት ለማገገም 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋታል ተባለ በኢትዮጵያ ከሁለት ዓመት በፊት ህወሀት በሀገር መከላከያ የሰሜን እዝ ላይ ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ ነበር ጦርነት የተነሳው። በዚህ ጦርነት ምክንያት 800 000 ዜጎች ህይወታቸው እንዳለፈ ሲገለጽ የግለሰቦች እና የመንግስት መሰረተ ልማቶች ወድመዋል። ጦርነቱ አሁን ላይ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሰላም ስምምነት ተፈርሞ ጦርነቱ ቆሟል። ይህ ለሁለት ዓመት የዘለቀው ጦርነት የወደሙ መሰረተ ልማቶችን እና ሌሎች ሀብቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የፋይናንስ ሚንስቴር ገልጿል። ጦርነቱ ክፉኛ የጎዳቸው ትግራይ ፣አማራ እና አፋር ክልሎች በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ከደረሰባቸው ጉዳት እንዲያገግሙ 20 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋልም ተብሏል። ይህ የመልሶ ግንባታ በጀት ከፌደራል መንግሥት ፣ ዓለም…
Read More
የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ለሁለት ሐኪሞች የህይወት ዘመን ሽልማትን አበረከተ

የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ለሁለት ሐኪሞች የህይወት ዘመን ሽልማትን አበረከተ

ማህበሩ 59ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ አካሂዷል። ማህበሩ በጉባኤው ላይ በህክምና ሙያ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለሰጡ ሁለት ሐኪሞች የህይወት ዘመን ሽልማትን አበርክቷል ። ዶክተር ይርጉ ገብረህይወት በወንድ ጾታ እንዲሁም ዶክተር ተቋም ደበበ ደግሞ በሴት የህይወት ዘመን ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ተሸላሚዎቹ በሕክምና ሙያቸው በአንጻራዊነት የተሻለ የሕክምና አገልግሎት እንደሰጡ በሽልማት ስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሕክምና ማህበር ከህይወት ዘመን ሽልማት በተጨማሪ ዶክተር ትህትና ንጉሴን በሴት ወጣት ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀኪም በሚል ሲሸልም ዶክተር ፈለቀ አግዋርን ደግሞ በወንድ ወጣት ተጽዕኖ ፈጣሪ ሀኪም ሲል ሸልሟል። አዲስ ህይወት የማገገሚያ ማዕከል ደግሞ የዓመቱ ምርጥ የጤና ተቋም በሚል ተሸልሟል። ሽልማቱን የጤና ጥበቃ ሚንስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እና የኢትዮጵያ…
Read More
ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ከሰሞኑ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በአዲስ አበባ የነበሩት ጌታቸው ረዳ በትግራይ አዲስ የሚቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ በሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ መመረጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ቪኦኤ) የትግርኛው አገልግሎት ክፍል እንደዘገበው፣ ጌታቸው የማዕከላዊ ኮሚቴውን አብላጫ ድምጽ አግኝተዋል። የቀድሞው የሕግ መምህር ጌታቸው ረዳ፣ በመንግሥት እና በሕወሓት መካከል በፕሪቶሪያ የሕወሓት  ዋንኛ ተደራዳሪ የነበሩ ናቸው። የሽግግር ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም እየተንቀሳቀሰች የምትገኘው ትግራይ ክልል፣ ከጦርነቱ አስቀድሞ በዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ስትመራ ነበር። ከሰሞኑ በወጡ ዘገባዎች የፌዴራሉ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትግራይ በደብረጽዮን መሪነት እንድትቀጥል አይፈልጉም። ዋሺንግተን ፖስት ይዞት በወጣው ዘገባ ዐቢይ ለትግራዩ ጦርነት መጀመር ደብረጽዮንን ይወቅሳሉ። የሕወሓት ሰዎች ከሰላም ስምምነቱ በኋላ…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ የካርጎ አገልግሎት ጀመረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዴንማርክ  ኮፐንሀገን ወደ አዲስ አበባ ሳምንታዊ  የእቃ ጭነት አገልግሎት በረራ ጀመረ።  የእቃ ጭነት በረራው  የሚደረገው  በቅርቡ ከመንገደኛ ወደ እቃ ጭነት አገልግሎት በተቀየረው ቦይንግ 767-300F አውሮፕላን እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ ሳምንታዊ እያንዳንዱ በረራ እስከ 45 ቶን ያህል ጭነት እንደሚጓጓዝ አየር መንገዱ ለኢትዮ ነጋሪ ገልጿል። ይህ አዲስ የእቃ ጭነት  አገልግሎት በአውሮፓ  እና በተቀረው  ዓለም መካከል  ያለውን የንግድ  እንቅስቃሴ የሚያሳልጥ ይሆናል ተብሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው ግንቦት ወር  ጀምሮ ወደ ኮፐንሀገን  የመንገደኛ በረራ  አገልግሎት እጀምራለሁ ብሏል። ይህ የመንገደኞች በረራ መጀመርም ተጨማሪ  የካርጎ  አገልግሎት አቅም ይፈጥርልኛል ብሏል። ይህ በዚህ እንዳለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ  ወደ  ኢንዶኔዢያ ዋና ከተማ ኩዋላላፑር ከተማ አዲስ በረራ እንደሚጀምር አስታውቋል። አየር መንገዱ ከመጋቢት 24,…
Read More
ግብጽ ኢትዮጵያን ከማስፈራራት እንድትታቀብ ተጠየቀች

ግብጽ ኢትዮጵያን ከማስፈራራት እንድትታቀብ ተጠየቀች

ግብፅ ኃላፊነት ከጎደለው ንግግር እና ማስፈራሪዎቿ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የህዳሴ ግድብን በተመለከተ “ሁሉም አማራጮች ክፍት ናቸው” በማለት የሰጡትን መግለጫ ኃላፊነት የጎደለው ንግግር ሲል ውድቅ አደረገ።ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ፥ ግብጽ የዓባይ ግድብን አስመልክታ ለኢትዮጵያ ማስፈራሪያ የታከለበት መግለጫ ሰጥታለች ብሏል፡፡ ይህም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር እና የአፍሪካ ህብረት ድንጋጌን በግልጽ የሚጥስ መሆኑን ገልጿል፡፡በተጨማሪም ይህ ድርጊት በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ራሷኑ ግብጽና ሱዳን በፈረንጆቹ መጋቢት 2015 ያደረጉትን ስምምነት የጣሰም ነው ብሏልሚኒስቴሩ በመግለጫው፡፡ በዚህም ግብጽ ተገቢ ያልሆኑና ህገወጥ መግለጫዎችን ከማውጣት እንድትቆጠብ አሳስቧል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘም የሚመለከታቸው አካላት ግብጽ የዓለም አቀፉ ግንኙነት ደንብን እየጣሰች መሆኗን ልብ…
Read More