CAF

ኢትዮጵያ የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ በፋዊ ጥያቄ አቀረበች

ኢትዮጵያ የ2028 የአፍሪካ ዋንጫን ለማስተናገድ በፋዊ ጥያቄ አቀረበች

​ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2028 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) ውድድር ለማስተናገድ ይፋዊ የጨረታ ጥያቄዋን ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ማቅረቧን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ሀገሪቱ ውድድሩን ለመጨረሻ ጊዜ ያዘጋጀችው በ1976 እንደመሆኑ መጠን፣ ጥያቄው ከተቀባይነት ካገኘ ከ50 ዓመታት በላይ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ትልቁን አህጉራዊ መድረክ ዳግም ይመልሳል። ​የ2028ቱ ውድድር ከአፍሪካ ዋንጫ የተለመደ ባለሁለት ዓመት ዑደት ተለውጦ በየአራት ዓመቱ መካሄድ የሚጀምርበት የመጀመሪያው ውድድር ይሆናል። 130 ሚሊዮን ሕዝብና የአፍሪካ ህብረት ዋና መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ዝግጁነቷን ብታረጋግጥም፣ በባህር ዳር እና በመዲናዋ የሚከናወኑ የስቴዲየም ግንባታዎች እንዲሁም የጸጥታ ስጋቶች በዝግጅት ሂደቱ ላይ የሚጠበቁ ተፎካካሪ ተደራራቢ ፈተናዎች ናቸው። ​በፊፋ ደረጃ 143ኛ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ እ.ኤ.አ. በ2027 ጎረቤቶቿ ኬንያ፣…
Read More
ባህርዳር ስታዲየም የካፍ እውቅና ተሰጠው

ባህርዳር ስታዲየም የካፍ እውቅና ተሰጠው

ባሕርዳር ስታዲየም ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ተፈቅዶለታል። የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መስፈርቶችን በማሟላት ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እንዲያካሂድ ፈቃድ አግኝቷል። ኢትዮጵያ የካፍ እና ፊፋ እውቅና ያለው ስታዲየም ባለቤት ባለመሆኗ ዋልያዎቹን ጨምሮ ክለቦች በውሰት ሜዳዎች ሲጫወቱ ቆይተዋል። የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም መስፈርቶችን ባለማሟላቱ ዓለምአቀፍ ጨዋታዎችን እንዳያደርግ አግዶት ቆይቷል። በዚህ ምክንያት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሌሎች ሀገራት እንዲጫወት ተገድዶ ቆይቷል። ካፍ የባሕርዳር ዓለም አቀፍ ስታዲዬም የዓለም አቀፍ ስታዲዬም ማሟላት የሚገባውን መስፈርት እንዲያሟላ አቅጣጫ ማስቀመጡ ይታወሳል። ባለፉት ዓመታት ስታዲዬሙ የካፍ መስፈርቶችን ባሟላ መልኩ ግንባታ ሲካሄድለት ቆይቶ አሁን ላይ መስፈርቶችን በማሟላቱ ማረጋገጫ ተሰጥቶታል ተብሏል። ኢትዮጵያ የካፍ…
Read More
ሴኔጋላዊው አል ሀጂ ዲዮፍ የዋናው ስፖርት ኩባንያ አምባሳደር ሆነ

ሴኔጋላዊው አል ሀጂ ዲዮፍ የዋናው ስፖርት ኩባንያ አምባሳደር ሆነ

የሴኔጋሉ የእግር ኳስ ኮኮብ አልሀጂ ዲዩፍ በኢትዮጵያ ላለ አንድ የስፖርት ትጥቅ አልባሳት አምራች ኩባንያ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል። ስምምነቱ በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን "ከአፍሪካ ምርጡ ትጥቅ አምራች ጋር ስምምነት ፈፅሜያለሁ “ ብሏል ዲዩፍ። ሴኔጋላዊው የቀድሞ ታሪካዊ ተጨዋች ኤል ሀጂ ዲዩፍ የኢትዮጵያው ትጥቅ አምራች ብራንድ ዋናው አምባሳደር በመሆን መሾሙን ኩባንያው ገልጿል። ታሪካዊው ተጫዋች የዋናው ስፖርት አልባሳት በሚመረትበት አዲስ አበባ ሀብቴ ጋርመንት እና ህትመትን ከጎበኘ በኋላ ስምምነት ፈፅሟል። “ ከአፍሪካ ምርጡ ትጥቅ አምራች ጋር ስምምነት ፈፅሜያለሁ “ ሲል ዲዩፍ ከጉብኝቱ በኋላ ተናግሯል። አክሎም  "በቀጣይ ከትልልቅ ታሪካዊ ተጫዋቾች ጄጄ ኦኮቻ ፣ ኑዋንኩ ካኑ ፣ አዲባየር እና ካሊዱ ፋዲጋን በማምጣት ዋናውን በአለም ገናነቱን እናሳየለን "…
Read More
የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ወሰነ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ ለማድረግ ወሰነ

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና አዲስ አበባ እንዲካሄድ መወሰኑ ይፋ ተደርጓል። ጉባዔው ዲሞክራቲክ ኮንጎ ላይ ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም በቅርቡ በተከሰተው የዝንጀሮ ፈንጣጣ ወረርሽኝ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መቀየሩን የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ ገልጸዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት ጉባኤው አዲስ አበባ ላይ እንዲካሄድ ጥያቄ አቅርቦ በካፍ ተቀባይነት ማግኘቱን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል። በዚህም መሰረት የካፍ ጠቅላላ ጉባዔ በቀጣይ ጥቅምት ወር በመዲናችን አዲስ አበባ ከተማ የሚካሄድ ይሆናል። ካፍ ዛሬ በሰጠው የቅድመ ጠቅላላ ጉባኤ ጋዜጣዊ መግለጫ የ2024 ቻን አፍሪካ ዋንጫ በሚቀጥለው የካቲት ወር በናይሮቢ ፣ ካምፓላ እና ዳሬ ሰላም እንደሚካሄድ አሳውቋል። የ2024 ቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጥቅምት እና…
Read More
ኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት እቅድ እንዳላት ገለጸች

ኢትዮጵያ የ2029 የአፍሪካ ዋንጫን የማዘጋጀት እቅድ እንዳላት ገለጸች

ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አመታት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድርን እንድታዘጋጅ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ ተናግረዋል። የአፍሪካ ዋንጫን እ.ኤ.አ በ2029 ወይም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሩ ለእቅዱ መሳካትም ቢያንስ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ካፍ ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ መስፈርቶችን በማስቀመጡ ኢትዮጵያ አንድም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እንዳይኖራት አድርጓል ሲሉም አቶ ቀጀላ መርዳሳ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የካፍን ደረጃ የሚመጥኑ ስታዲየሞች የሌላት በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዘም ላሉ ጊዜያት ከሀገሩ ዉጪ ለመጫወት ተገድዶ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። የዉድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ቢያንስ ስድስት ስታዲየሞችን እንዲያዘጋጁ ካፍ ቢያዝም ኢትዮጵያ እስካሁን የካፍን ደረጃ ያሟላ ስታዲየም የሌላት ሲሆን ውድድሩን ለማዘጋጀት እያደረገች ስላለው ዝግጅት የተባለ…
Read More
ዋሊያዎቹ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጉት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቀኑ

ዋሊያዎቹ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጉት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቀኑ

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ለሚያደርገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ወደ ሞሮኮ አቅንቷል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በኮትዲቯር አስተናጋጅነት በሚካሄደው 34ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ከጊኒ ብሔራዊ ቡድን ጋር የምድብ ማጣሪያ ጨዋታውን መጋቢት 15 እና 18 ቀን 2015 ዓ.ም በሞሮኮ ያደርጋል። የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ በማድረግ ከመጋቢት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ልምምዳቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዋልያዎቹ ከትናንት በስቲያ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከሩዋንዳ አቻቸው ጋር ባደረጉት የአቋም መለኪያ ጨዋታ በከነዓን ማርክነህ ግብ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወቃል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አራት ከግብጽ፣ ከማላዊና ከጊኒ ጋር ተደልድሏል፡፡ እስከአሁን…
Read More