27
May
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ 73 አባላትን ያቀፈ የአፍሪካ ኅብረት ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው የኢትዮጵያ ምርጫ 2018 ታዛቢ ልዑካን ቡድን ይመራሉ ተብሏል። በቀድሞው የኬኒያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው፣ የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ መግባቱን ኅብረቱ አስታውቋል። ታዛቢ ቡድኑ ከ37 አገራት የተውጣጡ 73 አባላትን ያቀፈ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ከታዛቢዎቹ ውስጥ 61 በመቶዎቹ ሴቶች እንደሆኑ ተገልጿል። የአፍሪካ ኅብረት የታዛቢዎች ቡድን የሚሰማራው ለአጭር ጊዜ ታዛቢነት ሲሆን፣ ጊዜያዊ ጽ/ቤቱን በስካይላይት ሆቴል እንደሚያደርግ አሳውቋል። ታዛቢዎቹ በሁሉም ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች እንደሚሰማሩም ተገልጿል። ሰባተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለማካሄድ ዝግጅቴን ጨርሻለሁ ያለው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአማራ ክልል በ8 የምርጫ ክልሎች ሊካሄድ የታሰበው ምርጫ መራዘሙን አስታውቋል። ቦርዱ…