Blog

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በሟቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በሟቋረጧ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጥ ብቻ 146 ሚሊየን ዶላር ማጣቷ ተነገረ ቶፕ 10 ቪፒኤን የቴክኖሎጂ ኩባንያ እንዳስታወቀው፣ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት ተከትሎ ለአንድ አመት ሙሉ የኢንተርኔት አገልግሎት በመዘጋቱ ሃገሪቱ 146 ሚሊዮን ዶላር ማጣቷን አስታውቋል። አሁንም ቢሆንም በመላው ሀገሪቱ ኢንተርኔት በመቋረጡ ሚሊዮን ዶላሮችን እያጣች ትገኛለች ብሏል። ኢንተርኔት ከተዘጋ ዛሬ 28ኛ ቀኑን የያዙ ሲሆን መንግሥት እስካሁን ስለጉዳዩ ያለው ነገር የለም። መንግሥት የዘጋውን የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲከፍት የተሉያዩ አካላት ግፊት በማድረግ ላይ ሲሆኑ የኢትዮጵያ ሚዲያ ምክር ቤት እና ኢሰመኮ ከሰሞኑ ኢንተርኔት እንዲለቀቅ ከጠየቁ ተቋማት መካከል ዋነኞቹ ናቸው። ኢትዮጵያ በዓለም ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት እቀባ ከሚፈጽሙ ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነች ኔትብሎክስ ከዚህ በፊት ባወጣው ሪፖርት ገልጿል። ቲክቶክ፣ዩቲዩብ፣ቴሌግራም…
Read More
ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

ኡጋንዳውያን የዓለም ፍጻሜ ደርሷል በሚል ወደ ኢትዮጵያ መፍለሳቸው ተገለጸ

በመቶዎች የሚቆጠሩ የኡጋንዳ የሐይማኖት ኑፋቄ አባላት የምፅዓት ቀንን በመስጋት ወደ ኢትዮጵያ እየተሰደዱ ነው ተብሏል፡፡ የኑፋቄ መሪዎቹ የዓለም መጨረሻ እንደቀረበና ሞትም አካባቢያቸውን እንደሚመታ አሳምኗቸዋል። በኡጋንዳ ምስራቃዊ ክፍል ውስጥ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸውን የኡጋንዳ ፖሊስ አስታወቋል። ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኑፋቄው አባላት ከአካባቢያቸው ይጀመራል ብለው ካመኑበት የዓለም ፍጻሜ ለማምለጥ ሸሽተዋል ብሏል። የኑፋቄው አባላት በቅርቡ አካባቢያቸው በሞት እንደሚመታ እና ሁሉም ሰዎች እንደሚሞቱ በመሪዎቹ እንደተነገራቸው ገልፀዋል። ንብረታቸውን ሸጠው ወደ ኢትዮጵያ መሰደዳቸው የተነገረው አነዚህ ኡጋንዳውያን ከዚያም ካሉበት በኡጋንዳ ከሚገኙ አንዳንድ ዘመዶቻቸው ጋር እየተነጋገሩ ነው። “የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ቤተክርስቲያን በሚባል የሃይማኖት ኑፋቄ ላይ በኡጋንዳ ምስራቃዊ ሴሬሬ ወረዳ በኦቡሉም መንደር ውስጥ የሚገኘውን የሃይማኖት ክፍል…
Read More
በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት በሚያደርጉ ህሙማን ላይ 50 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ተደረገ

በኢትዮጵያ የኩላሊት እጥበት በሚያደርጉ ህሙማን ላይ 50 በመቶ የዋጋ ጭማሪ ተደረገ

በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የኩላሊት ህሙማን ቁጥር በርካቶችን ለችግር እየዳረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል ። የህሙማኑን አቅም እየፈተነ የሚገኘው አቅምን ያላገናዘበ የህክምና ወጪ የብዙዎችን ቤት እያንኳኳ ይገኛል ሲሉ የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ተናግረዋል። በአሁኑ ሰዓት በዳግማዊ ሚኒሊክ ፣ በዘውዲቱ እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች 180 ህሙማን የነፃ ህክምና አገልግሎት እየተጠቀሙ ቢሆን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህሙማን ዕድሉን ባለማግኘታቸው ችግር ላይ መውደቃቸውን አቶ ሰለሞን ጠቁመዋል። እነዚህ ህሙማን ከእዚህ ቀደም በግል የህክምና ተቋማት ለአንድ ጊዜ የኩላሊት እጥበት ይጠየቁ ከነበረው ክፍያ እስከ 50 ከመቶ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ስራ አስኪያጁ ያነሱ ሲሆን በግል የህክምና ተቋማት ለአንድ ጊዜ እጥበት ይጠይቅ…
Read More
ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺህ ሴቶችን ወደ ሳውዲ አረቢያ ልትልክ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገር ልትልክ ነው በኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት 500 ሺሕ ሴቶችን ወደ አረብ አገራት በተለይም ወደ ሳውዲ አረቢያ ለሥራ ለመላክ በመንግሥት እቅድ መያዙ ተገለጸ፡፡ ይህን ተከትሎም በአማራ ክልል ኹሉም ዞኖች ሰሞኑን ወደ አረብ አገር ሄደው መስራት ለሚፈልጉ ወጣት ሴቶች ስልጠና ሊሰጥ መሆኑን ኢትዮ ነጋሪ ሰምታለች፡፡ ለአብነትም በምስራቅ ጎጃም ዞን ሦስት የስልጠና ማዕከላት የተዘጋጁ ሲሆን፣ በሞጣ፣ ደብረ ማርቆስ እና ደጀን ከተሞች ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ ሴቶች የቤት አያያዝና ሌሎች አስፈላጊ የሥራ ስልጠናዎች እንደሚሰጡኢትዮ ነጋሪ ከዞኑ መረጃ አግኝታለች፡፡ ስልጠናው ለ20 ቀን በመንግሥት በነጻ የሚሰጥ መሆኑን የተገለጸ ሲሆን፤ ከስልጠናው በኋላ ፈቃደኛ የሆኑ ሴቶች ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚያቀኑበት የዚህ…
Read More
የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አቪየሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ አደገ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ በማደግ በኤሮስፔስ እና በተለያዩ የሆቴልና ቱሪዝም ዘርፎች በቅድመ ምረቃ እና ድሕረ ምረቃ ፕሮግራሞች ማስተማር ጀመረ። የአቪዬሽን አካዳሚ የአቪዬሽን ስልጠና ፕሮግራሞችን በአብራሪነት፣ የአውሮፕላን ቴክኒሻን፣ የካቢን ሰራተኛ፣ የአየር መንገድ ሽያጭ እና አገልግሎት እና ሌሎች ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቷል።  ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ካደገ በኋላ በኤሮኖቲካል ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአውሮፕላን ጥገና ኢንጂነሪንግ በቢኤስሲ ዲግሪ፣ በአቪዬሽን ማኔጅመንት ቢኤስሲ ዲግሪ፣ በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ማኔጅመንት ቢኤ ዲግሪ እና ኤምቢኤ በአቪዬሽን ማኔጅመንት የመሳሰሉ የዲግሪ መርሃ ግብሮችን ጀምሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት "ከቀጣይ እድገትና ኢንቨስትመንት በኋላ 65 ዓመት ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ አቪዬሽን አካዳሚ ወደ ዩኒቨርሲቲ ደረጃ ማደጉ…
Read More
ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ

ዘምዘም ባንክ ከሀገር እና ውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ለመዋሃድ ዝግጁ መሆኑን ገለጸ የኢትዮጵያ የባንክ ህግ መሻሻሉን ተከትሎ በቅርቡ ወደ አገልግሎት የገባው ዘምዘም ባንክ የተሻለ ገቢ እና ተወዳዳሪ ለመሆን ከሌሎች ባንኮች ጋር ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ የባንክ ታሪክ ሙሉ ለሙሉ የእስላሚክ ባንክ አገልግሎትን በመስጠት ቀዳሚ የሆነው ዘምዘም ባንክ ከማንኛውም የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገራት ባንኮች ጋር ተዋህዶ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን የባንኩ ፕሩዝዳንት ወይዘሮ መሊካ ለኢትዮ ነጋሪ በድሪ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዝዳንቷ አክለውም ዘምዘም ባንክ ስራ ከጀመረበት ሰኔ 2013 ዓ.ም ጀምሮ በ54 ቅርንጫፎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡ ባንኩ ሙሉ ለሙሉ ወለድ አልባ የሆኑ ሁሉንም የፋይናንስ አገለግሎቶችን በመስጠት ላይ መሆኑን የተናገሩት…
Read More
የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

የአንድ ኪሎ ሽንኩርት ዋጋ ከሥጋ ከሁለት እጥፍ በላይ የተወደደባት አገር

ለምግብ ማጣፈጫነት ከሚውሉ አትክልቶች መካከል ሽንኩርት አንዱ ነው። ሽንኩርት በዓለም ዙሪያ መሠረታዊ የምግብ ግብአቶች ከሆኑት መካከል ይጠቀሳል። በበርካታ አገራት ሽንኩርት በድሃውም ሆነ በሃብታሙም ቤት የሚገኝ የምግብ አካል ሲሆን፣ ሥጋ ደግሞ እንደ ቅንጦት ምግብ የሚታይ ነው። በፊሊፒንስ ግን ይህ በተቃራኒ ሆኗል፤ የሽንኩርት ዋጋ የትኛውንም አይነት ሥጋ ለመግዛት ከሚወጣው ገንዘብ በበርካታ እጥፍ ይበልጣል። ለፊሊፒን ዜጎች ባለፉት ሳምንታት ጊዜ ሽንኩርት መሸመት ቅንጦት ሆኗል። ዋጋው በማሻቀቡ የተነሳ የሽንኩርት መግዣ ከሥጋ መግዣ በእጅጉ ንሯል። በዚህ ሳምንት ፊሊፒንስ ውስጥ አንድ ኪሎ ሽንኩርት 11 ዶላር (600 ብር ገደማ) ሲሆን፣ የአንድ ሙሉ ዶሮ ሥጋ ግን 4 ዶላር (220 ብር ገደማ) ብቻ ነው። የሽንኩርት ዋጋ ንረት የፈጠረውን የገበያ ክፍተት…
Read More
ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

ሩሲያ በክሬሚያ የጦር መሳሪያ ማከማቻ ስፍራ ላይ የደረሰዉ ፍንዳታ በሴራ ነዉ ስትል ተናገረች

የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በሰሜናዊ ክሬሚያ በሚገኝ ወታደራዊ መጋዘን የደረሰውን ፍንዳታ ተከትሎ ከ3,000 በላይ ሰዎችን አካባቢዉን ለቀው እንዲወጡ ያስገደደ ሲሆን የሴራ ዉጤት ነዉ ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ማስታወቁን የሩሲያ መንግስት ሚዲያ ዘግቧል። በትላንትናዉ እለት የደረሱት ፍንዳታዎች በሜይስኮዬ መንደር አቅራቢያ በሚገኘው የጥይት ማከማቻ ቦታን ያናወጡ እና የባቡር አገልግሎቶችን እንዲሁም የሃይል አቅርቦቶችን ያስተጓጎለ ነበር፡፡ በፍንዳታው በሰው ላይ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ ሚኒስቴሩ አክሏል።የሩሲያ ኮምመርሰንት ጋዜጣ በትላንትናዉ እትሙ በክሬሚያ ተጨማሪ ጥቃት ሊፈጸም እንደሚችል ዘግቧል፡ እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው በግቫርዴስኮዬ ባሕረ ገብ መሬት ላይ በሚገኘው የሩሲያ ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ጭስ መታየቱን ጽፏል፡፡ባለፈው ሳምንት በክሬሚያ በሩሲያ ስር በሚተዳደረው የአየር ጣቢያ ላይ የደረሰ ፍንዳታ የነበረ ሲሆን ሞስኮ በወቅቱ…
Read More
የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ ታሠረ

የቀድሞው የዚምባብዌ ፕሬዝደንት ሮበርት ሙጋቤ ወንድ ልጅ ሃራሬ ውስጥ በተዘጋጀ ድግስ ላይ ንብረት አውድሟል ተብሎ በቁጥጥር ሥር ዋለ። 31 ዓመቱ እንደሆነ የሚገመተው ሮበርት ሙጋቤ ጁኒዬር ሶስት ንብረት የማውደም እና ሁለት ፖሊስ የመተናኮስ ክስ ቀርቦበታል ሲሉ ጠበቃቸው ተናግረዋል። በድግሱ ላይ የመኪናዎች መስታወት ሲረግፍ አንድ የፖሊስ መኮንን ላይ ምራቅ መተፋቱ ተሰምቷል። የሙጋቤ ልጅ የቀረበበትን ክስ አጣጥሎ ከደሙ ንፁሕ ነኝ ይላል። አሁን ከእሥር ተለቆ ክሱን በድርድር ለመፍታት እየጣረም እንደሆነ ተነግሯል። ፖሊስ በትዊተር ገፁ እንደገለጠው የሮበርት ሙጋቤ ልጅ ጓደኛ የሆነው ሲንዲሶ ንካታዞ ያቀረበውን ቅሬታ ተከትሎ ነው ፖሊስ ወደ ሥፍራው ያቀናው። በድግሱ ላይ የደረሰው የንብረት ውድመት በገንዘብ ሲሰላ 12 ሺህ ዶላር አካባቢ ሊደርስ እንደሚችል ፖሊስ…
Read More
በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በወልቂጤ ግድያ የፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች በሕግ ይጠየቁ በሚል ነዋሪዎች አድማ መቱ

በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ እና የውሃ ጥያቄያቸውን ለማቅረብ አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የተኮሱ የፀጥታ ኃይሎች ለፍርድ እንዲቀርቡ በመጠየቅ ከቤት ያለመውጣት አድማ መምታታቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። ከቤት ያለመውጣት አድማው ከተጀመረ ቀናት መቆጠራቸውን የተናገሩት ነዋሪዎች የከተማዋ እንቅስቃሴም ሙሉ በሙሉ ተገድቧል ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። በከተማዋ ለወራት የተቋረጠው የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር እንዲፈታ ለመጠየቅ ባለፈው ሳምንት ጄሪካን ይዘው አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ የፀጥታ ኃይሎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን እና ቢያንስ 30 ሰዎች የአካል ጉዳት መድረሱን ነዋሪዎች እና ኢሰመኮ ማስታወቃቸው ይታወሳል። በከተማዋ ትራንስፖርት፣ የባንክ አገልግሎት፣ የመገበያያ መደብሮችም ሆነ የትኞቹም የመንግሥት ተቋማት ተዘግተው ከተማዋ ጭር ብላ መሰንበቷን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ሰኞ ምሽት…
Read More