01
Mar
ከዓመት ከስድስት ወር በኋላ የሚካሄደውን የፓሪስ ኦሊምፒክ እስከ 40 አገራት ያክል አድማ ሊመቱ እንደሚችሉ ፖላንድ አስጠነቀቀች። የፖላንድ የስፖርት እና ቱሪዝም ሚኒስትር ካሚል ቦርትኒዙክ የፓሪስ ኦሊምፒክ ትርጉም አልባ ሊሆን ይችላል ብለዋል። ይህ የሚስትሩ አስተያየት የተሰማው ዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ በፓሪሱ 2024 ኦሊምፒክ የሩሲያ እና ቤላሩስ ዜጋ አትሌቶች እንዲሳተፉ ለመፍቀድ ማቀዱን ፖላንድ፣ ሊቱኒያ፣ ኢስቶኒያ እና ላትቪያ በጋራ መቃወማቸውን ተከትሎ ነው። ዩክሬን የሁለቱ አገራት አትሌቶች የሚሳተፉ ከሆነ በውድድሩ አልገኝም ብላለች። የኦሊምፒክ ኮሚቴው ግን በውድድሩ ላይ አድማ ማድረግ ትርፉ “አትሌቶችን መቅጣት ብቻ ነው” ብሏል። የፖላንድ የስፖርት እና የቱሪዝም ሚንስትሩ የዓለም አቀፉ የኦሊምፒክ ኮሚቴ ከሳምንት በኋላ ከሚያደርገው ስብሰባ በፊት ግሬት ብሪቴን፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ካናዳን…