Mekele

ጦርነት እና የማህበራዊ መረዳጃ ተቋማት ስብራት በትግራይ

ጦርነት እና የማህበራዊ መረዳጃ ተቋማት ስብራት በትግራይ

በሀገራችን ኢትዮጵያ ተሰባስቦ ተረዳድዶና ተደጋግፎ መኖር በአጠቃላይ ማህበራዊ ሕይወት አንዱ የሕይወት ዑደት ነው።  ታዲያ ይህ የመረዳዳት ሒደት ደስታን ሐዘንን እንዲሁም የጤና እክልን መሠረት በማድረግ የሚከወን ነው በተለይም እድር እና እቁብን እንደ ምሳሌ ብንወስድ ኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ የሚባሉ እና ማህበረሰቡ ጠብቆና አክብሮ የያዛቸው መረዳጃ እና መደጋገፊያ ሕብረቶችናቸው። ታዲያ እነዚህ ሕብረቶች በአንድም በሌላም መልኩ እክል ሲገጥማቸው አሊያም የመፍረስ አደጋ ሲጋረጥባቸው ለመታደግ ጊዜ የሚፈጅ እና አስቸጋሪ ይሆናል። በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮሮና ወረርሺኝ እንዲህ ያሉ መረዳጃ ማህበራትን ለማጥፋት አሊያም ለማቀዝቀዝ ዋነኛ ምክንያቶች ሆነዋል። በመቀሌ ከተማ የሚገኝ ትልቅ እድር ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ለተኪዳን በነዚህ ሁለት አጋጣሚዎች የተፈጠረውን የእድሩን ከፍተኛ መቀዛቀዝ ሲገልጹ…
Read More
ኑሮ ውድነት በመቀሌ ምን ይመስላል?

ኑሮ ውድነት በመቀሌ ምን ይመስላል?

በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንያት ከተጎዱ ክልሎች መካከል አንዱ ትግራይ ሲሆን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎች ከመሞታቸው በተጨማሪ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፡፡ ይህ ጦርነት በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ጦርነቱ የቆመ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዳግም ስራ ጀምረዋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳድር ከተቋቋመ በኋላ ከፌደራል መንግስት እና ከሌሎች መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ተጎጂዎችን ለመርዳት እየተሰራም ይገኛል፡፡ ቀስ በቀስ ህይወት በትግራይ ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት ሁኔታ ለመመለስ የተለያዩ ጥረቶች እየተካሄዱ ሲሆን ኢትዮ ነጋሪ ወደ ክልሉ አምርታ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ምልከታ አድርጋለች፡፡ ከታዘብናቸው ጉዳዮች መካከል ህይወት በትግራይ መዲና መቀሌ ምን ይመስላል? የሚለው ሲሆን የኑሮ…
Read More
የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ ቅሬታዎችን ማየት እንዳልቻለ ተናገረ

በትግራይ ክልል ጦርነት የቆመ ቢሆንም ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሶ መስራት አደጋች ሆኗል ተብሏል፡፡ በክልሉ ከመልካም አስተዳድር ጥያቄዎች ይልቅ የምግብ ጉዳይ ዋነኛው ችግር እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት ዓመት በቆየው ጦርነት ምክንት ስራ አቁሞ ከነበሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠበቃ ተቋም መቀሌ ቀርንጫፍ አንዱ ነበር፡፡ ይህ ጦርነት በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው የፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ጦርነቱ የቆመ ሲሆን አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም ዳግም ስራ ጀምረዋል፡፡ ከታህሳስ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ሥራውን በአዲስ መልክ የጀመረው የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መቀሌ ቅርንጫፍ በበጀት እጥረት ምክንያት ጉዳዮችን ለመመልከት አዳጋች እየሆነበት እንደመጣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ደጋፊት ረዳ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል። ተወካይዋ እንዳሉት…
Read More
የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

የተመድ ፈንጅ አምካኝ ቢሮ በትግራይ ክልል ቢሮ ሊከፍት መሆኑን አስታወቀ

በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ መቆሙ ይታወሳል፡፡ በዚህ ጦርነቱ ምክንያት ተቋርጠው የነበሩ አገልግሎቶች ወደ ነበሩበት እንዲገቡ የማድረግ ስራ በፌደራል እና ክልል መንግስታት እየተሰራም ይገኛል፡፡ ይሁንና በጦርነቱ ወቅት በየቦታው ተቀብረው የነበሩ ፈንጂዎች ትምህርትን እና ሌሎች አገልግሎቶችን ማስቀጠል አልቻሉም ተብሏል፡፡ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሰሜን ኢትዮጵያ ቦታዎች ያሉ ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ፈቃድ ተሰጥቶታል ተብሏል፡፡ እንደ አፍሪካ ህብረት መግለጫ ከሆነ ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በመሰማራት…
Read More
መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል መባሉን አስተባበለ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል መባሉን አስተባበለ

መቐለ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ይጀምራል በሚል የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀበሰሜን ኢትዮጵያ ሲካሄድ በነበረው ጦርነት ምክንያት የመማር ማስተማር ሥራው የተቋረጠው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ሥራውን እንደሚጀምር በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘገብ ቆይቷል። በዚህም ዩኒቨርሲቲው በሚቀጥሉት አራት ወራት 24 ሺሕ የሚጠጉ የቀድሞ ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ እና ከመስከረም ወር 2016 ጀምሮ አዲስ ተማሪዎችን እንደሚቀበል የተገለጸ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው በመንግሥት በኩል የሚያስፈልግ በጀት ሁሉ እንደተለቀቀለትም ተነግሯል። ነገር ግን ይህ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን የዩኒቨርስቲው ሰራተኞች እና አመራሮች አረጋግጠዋል። መቐለ ዩኒቨርሲቲም ይህንን ዜና የሚመለት መረጃ በይፋዊ የፌስቡክ እና የትዊተር አካውንቱ ላይ አላወጣም። የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ፋና ሓጎስ ዩኒቨርሲቲው ሥራ ለመጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር…
Read More