ethiopiapolitics

የምርጫ ቦርድ አዲስ አሰራር ተፅዕኖ እንደሚፈጥርባቸዉ ፓርቲዎች አስታወቁ

የምርጫ ቦርድ አዲስ አሰራር ተፅዕኖ እንደሚፈጥርባቸዉ ፓርቲዎች አስታወቁ

ስምንት የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ የዘረጋው አዲስ አሰራር በቀጣዩ ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥርባቸው አስታውቀዋል። የቦርዱን አዲስ አሰራር የተቃወሙ ፓርቲዎች የህብር ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ  ፓርቲ (ህብር ኢትዮጵያ)፣ መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ( ባልደራስ) ትብብር ለኢትዮጵያ  አንድነት ፓርቲ፣ለኢትዮጵያ አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ)፣የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ (ዎብን) ፓርቲዎች ናቸው። በዚህ በጋራ መግለጫቸው የሀገሪቱ አቅም ባልፈቀደበትና እንደ ሀገር  ግንዛቤ በሌለበት ቴክኖሎጂካል አሰራር  ለመስፈርትነት መጠቀም አግባብነት የለውም ብለዋል። አካል ጉዳተኞች ከሁለት ሆስፒታሎች ማስረጃ እንዲያቀርቡ ግዴታ መቀመጡ፣ የአገሪቱን ገጠር አካባቢዎች ያላገናዘበና ሆስፒታሎች በሌሉበት ማስረጃ  መጠየቅ የአካል ጉዳተኞች ነባራዊ ሁኔታ የሚዳሰስና የሚታይ ሆኖ ሳለ ማስረጃ መጠየቁ በራሱ…
Read More
በኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳሩ ወደ አስቸጋሪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ የፓለቲካ ምህዳሩ ወደ አስቸጋሪ ምዕራፍ እየተሸጋገረ መሆኑ ተገለፀ

በኢትዮጵያ የስነ መንግስት ታሪክ ውስጥ ኢትዮጵያ አሁን የምትገኝበት የፓለቲካ ምዕራፍ እጅግ  አስቸጋሪ ደረጃ ላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርታ (ኢዜማ) ዋና ፀሐፊ አበበ አካሉ ገልፀዋል። አቶ አበበ አካሉ ይሄን በእናት ፓርቲ አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዳሉት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ አስቸጋሪ ሁኔታ እየገባ ነው። በኢትዮጵያ እየተሸጋገረ የመጣውን አደገኛ የፓለቲካ ምዕራፍ በተበታተነ ትግል ውስጥ መቀልበስ እንደማይቻልም አቶ አንስተዋል። አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ዴሞክራሲ ቅንጦት ነው የሚሉት አቶ አበበ ሰውነት እጅግ የረከሰበት ዘመን ላይ መድረሳቸውን አስታውሰዋል። አክለውም የአገር እሴት ሲናድ አብሮ የሚናድ አገረ መንግስት ምስረታ በመኖሩ የሀገርን ቋሚ እሴት'ና ምዕተ አመት ዘለል ተቋማት መከበር አለባቸው ብለዋል። ምንም እንኳን እንደ ፓርቲ ህገመንግስቱ እንዲቀየር…
Read More
ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዳያካሂዱ መከልከላቸውን ምርጫ ቦርድ አወገዘ

ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዳያካሂዱ መከልከላቸውን ምርጫ ቦርድ አወገዘ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባዔያቸውን እንዳያካሂዱ መከልከሉን አወገዘ። ቦርዱ ባለፈው ሳምንት ጠቅላላ ጉባዔያቸውን እንዳያካሂዱ የተከለከሉትን ፓርቲዎች አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። ቦርዱ በመግለጫው ፓርቲዎች ጉባዔ እንዳያካሄዱ የከለከሉት እነማን እንደሆኑ እንዳላወቃቸው ገልጾ ነገር ግን እገዳውን የጣሉት አካላት የህግ አስፈፃሚ ሃላፊዎች ትእዛዝ እንደሆኑ አስታውቋል። እናት ፓርቲ፣ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲና አዲስ የተመሰረተው ለጉራጌ አንድነትና ፍትህ (ጎጎት) ፓርቲዎች ባሳለፍነው ሳምንት የፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያደርጉ በጸጥታ አካላት መከልከላቸውን የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚዴቅሳ ተናግረዋል። በመግለጫውም በፓርቲዎቹ ላይ የደረሰው ወከባ ከህግ አንፃር ትክክል አለመሆኑን ገልፀው ፤በቀጣይም ይህን ችግር የፈጠሩ አካላትን አጣርቶ ማቅረብ የፍትህ አካላት ስራ እንደሆነ ገልቷል። አዲስ የተመሰረተው የጎጎት ፓርቲ አመራሮችም መታሰራቸውን የተናገሩት የምርጫ…
Read More