Abebebikila

ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

ጃፓን ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ሰየመች

በጃፓን ካሳማ ከተማ ለአትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መንገድ ተሰየመ በጃፓን ካሳማ ከተማ አትሌት አበበ ቢቂላን ለማስታወስ የግማሽ ማራቶን መንገድ በስሙ መሰየሙን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። የስያሜ ስነ-ስርዓቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበልን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራን፣ በጃፓን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌን እና የካሳማ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ በርካታ ባለስልጣናት በተገኙበት ተከናውኗል። በስነ-ስርዓቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ይህ የመታሰቢያ ስያሜ ለአትሌቱ ክብር ከመስጠት በተጨማሪ በኢትዮጵያ እና በጃፓን መካከል ያለውን ጥብቅ ወዳጅነት እና የባህል ትስስር የሚያሳይ እንደሆነ ገልጸዋል። አትሌት አበበ ቢቂላ በ1964ቱ የቶኪዮ ኦሎምፒክ ያገኘው ድል ኢትዮጵያን ያስጠራ ብቻ ሳይሆን በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ግንኙነትም አጠናክሯል ብለዋል። በጃፓን…
Read More
ኢትዮጵያዊው አበበ ቢቂላን ለማሰብ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያዊው አበበ ቢቂላን ለማሰብ ሮም ላይ በባዶ እግሩ ሊሮጥ መሆኑን አስታወቀ

የፊታችን እሁድ መጋቢት 10 ቀን 2015 ዓ.ም የ2023 የሮም ማራቶን ይካሄዳል። በዚህም ማራቶን ታሪክ ራሱን ይደግማል የተባለ ሲሆን ኢትዮጵያዊው የባዶ እግር ሯጭ እንዲሁም ለረጅም አመታት በኢትዮጵያ ታላቁ ሩጫ ቁልፍ ዳይሬክተር በመሆን የሰራው የ45 ዓመቱ ኤርሚያስ አየለ ሙሉ ማራቶን በባዶ እግሩ ይሮጣል። ኤርሚያስ አየለ ይህንን የሚያደርገው ለኢትዮጵያው ታላቅ አትሌት አበበ ቢቂላ ክብር እንዲሁም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ሲል ነው። " አበበ ቢቂላ በኦሎምፒክ ጨዋታዎች የወርቅ ሜዳሊያ በማግኘት የመጀመሪያው ጥቁር በመሆኑ ለኢትዮጵያውያን አትሌቶች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ለአፍራካውያን ስኬት መሰረት ጥሏል " የሚለው ኤርሚያስ " ሆኖም ግን ለሰራው ታሪክ የሚገባውን ያህል እውቅና እንዳላገኘ ይሰማኝ ነበር " ብሏል። ኤርሚያስ ፤ የአትሌት አበበ ቢቃላ ታሪክ ሁሌም…
Read More