Blog

በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ወራት ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር መፍረሱ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ባለፉት 6 ወራት ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር መፍረሱ ተገለጸ።

ባለፉት 6 ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ከ1ሺህ 300 በላይ ትዳር በፍቺ መጠናቀቃቸው ተገለጸ። በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት 1ሺህ342 ፍቺዎች እና 14ሺህ 136 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል። ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ የተመዘገበው የፍቺ ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጻር ተቀራራቢ ሲሆን፤ በ2014 በጀት ዓመት 1 ሺህ 623 የፍቺ ምዝገባዎች መደረጋቸውን መረጃዎች ያመለክታሉ። በአዲስ አበባ ከ2012 እስከ 2014 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ 16 ሺህ 35 ፍቺዎች እንደተካሄዱ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ መረጃ ያሳያል። የወሳኝ ኩነት ምዝገባና ማስረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ቤቴልሔም እንደሚገልጹት መረጃዎቹ የሚያመላክቱት በመስሪያ ቤቱ በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡትን ብቻ ነው።…
Read More
መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

መንግሥት በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ በድጋሚ ተጠየቀ

የኢትዮጵየ መንግሥት ፌስቡክ እና ዩቲዩብን ጨምሮ በማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ላይ የጣለውን ገደብ እንዲያነሳ የጠየቀው ዓለም አቀፉ መብቶች ተሟጋች አምነስቲ ኢንተርናሽናል ነው፡፡  አምነስቲ የማኅበራዊ መገናኛ መድረኮቹ ከተገደቡ አንድ ወር እንደሞላቸው ዛሬ ሐሙስ የካቲት 30፣ 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ላይ አስታውቋል፡፡  በጉዳዩ ላይ የተናገሩት የአምነስቲ የምሥራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ፍላቪያ ምዋንጎቪ፤ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ እና ዩቲዩብን ማኅበረሰቡ እንዳይጠቀም ገደብ ከጣሉ አንድ ወር እንደሞላቸው አስታውሰው፤ ይህም ‹‹የዜጎችን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽና መረጃን የማግኘት መብቶችን በግልጽ የሚጥስ ነው›› ብለዋል፡፡  በኢትዮጵያ አምነስቲ የጠቀሳቸው የማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ገደበ የተጣለባቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረ ክስተት ተከትሎ ውጥረት በመስፈኑ ነበር፡፡  የመብቶች ተሟጋቹ በመግለጫው…
Read More
በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ ፖሊሶች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

በአዲስ አበባ በዓድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ህግ በጣሱ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ። በዘንድሮው የአድዋ በኣል በአዲስ አበባ ምኒልክ አደባባይ የጸጥታ ሀይሎች በዜጎች ላይ ያልተገባ ድርጊት መፈጸማቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ እና ሌሎችም ተቋማት መናገራቸው ይታቀሳል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዪ ዙሪያ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በዕለቱ የህግ ጥሰት በፈጸሙ የፖሊስ አባላት ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል። ኮሚሽኑ አክሎም በዓሉ በተከበረበት እለት የከተማዋን ሰላም አውከዋል በሚል 878 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ብሏል። በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት ውስጥም 557ቱ ከሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ መሆናቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን…
Read More
<strong>በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ</strong>

በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ

በኢትዮጵያ 22 ሚሊዮን ሴቶች የወር አበባ ንጽህና መጠበቂያ እንደማያገኙ ተገለጸ በኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት የተከሰቱ ሰው ሰራሽ የተፈጥሮ ችግሮች የተነሳ ቁጥራቸዉ ከፍተኛ የሆኑ ዜጎች ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ ጋር ተያይዞ በሚነሱ ችግሮች በከፍተኛ ሁኔታ ሰላባ የሚሆኔት ሴቶች መሆናቸውን ጥናቶች ያመላክታሉ።ይህንኑ ተከትሎ በኢትዮጵያ የወር አበባ ከሚያዩ ከ35 ሚሊዮን በላይ ሴቶች ውስጥ 22 ሚሊዮን ያህሉ የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ እንደማያገኙ የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች ወይዘሮ ሚካል ማሞ ተናግረዋል። 22 ሚሊዮን ያህሉ ምንም አይነት ስለ ንጽህና መጠበቂያ መረጃ የማያገኙ መሆናቸውን የሚያስረዱት ሚካል ይህዉ ቁጥር በቀጣይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ስጋታቸዉን ገልጸዋል።ይህንን አስመልክቶ የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ ድርጅት ዘላቂ የንጽህና መጠበቂያ ምርቶችን በማምረት ላይ…
Read More
መንግስት አራት ድርጅቶችን ወደግል ሊያዛውር መሆኑን ገለጸ

መንግስት አራት ድርጅቶችን ወደግል ሊያዛውር መሆኑን ገለጸ

መንግስት አራት ድርጅቶችን ወደግል ለማዛወር ማቀዱ ተገለጸ መንግስት የተወሰኑ ተቋማትን ወደግል የማዛወር እቅድ እንዳለው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃብታሙ ኃይለሚካኤል በሰጡት ማብራሪያ፤ በመንግስት የአክሲዮን ድርሻ ተይዘው ያሉ ተቋማት አሉ፡፡ እነርሱን ባለሃብቶች እንዲገቡበት ይፈለጋል ብለዋል፡፡ በመንግስትና በግል አጋርነት ያሉ እንደ ቢ.ኤም ጨርቃጨርቅ፣ አፍሪካ ጁስ፣ አብያታ ሶዳ አሽ እና አምቼ በሂደት ወደግል ባለሀብቶች ለማዛወር መታቀዱን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። መንግስት ባለፉት ዓመትት 300 በላይ ድርጅቶችን ወደግል ማዛወሩን ጠቁመው፤በአሁኑ ወቅትም የመንግስትን እና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረገ መልኩ የነበረው አሰራር የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ፣ ብሔራዊ እንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ…
Read More
ከኢትዮጵያ የተዘረፉ 538 ቅርሶች በእንግሊዝ ተገኙ

ከኢትዮጵያ የተዘረፉ 538 ቅርሶች በእንግሊዝ ተገኙ

ከኢትዮጵያ የተዘረፉ 538 ያህል ቅርሶች በእንግሊዝ ተገኙ ከኢትዮጵያ የተዘረፉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ባሕላዊ ቅርሶች በእንግሊዝ እንደሚገኙ ተገለጸ፡፡ ቅርሶቹ እንግሊዝ ኢትዮጵያን በፈረንጆቹ 1868 ላይ በወረረችበት ወቅት በወታደሮች መዘረፋቸውም ተጠቁሟል፡፡ “ዘ ፕሪንስ ኤንድ ዘ ፕላንደር” ወደ አማርኛ ሲመለስ “ልዑሉ እና ዘረፋው” የተሠኘ መፅሐፍ የደረሱት እንግሊዛዊው አንድሪው ሄቨንስ 538 ያህል የኢትዮጵያ ቅርሶች እንዴት ወደ እንግሊዝ እንደተወሰዱ በመፅሐፉ በዝርዝር አመላክተዋልም ነው የተባለው፡፡ ደራሲው ቅርሶቹ በለንደን እንደሚገኙ መጠቆማቸውንም ኤቭኒንግ ስታንዳርድ የተሰኘው የሀገሪቷ የዜና ምንጭ ዘግቧል። የጠቀሷቸው ቅርሶች ከጥቃቅን እና ከተቀደሱ መፅሐፍት እና ቅርሶች ጀምሮ የከበሩ መዋቢያ የዕጅ አምባሮች ፣ የነገሥታት አልባሳት ፣ የነገሥታት የጋብቻ አልባሳት ፣ ዘውድ እና ታቦታት ይገኙበታል፡፡ የእንግሊዝ ወታደሮች ቅርሶቹን በያዟቸው ቦርሳዎች እና…
Read More
ቻይና ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጠች

ቻይና ከ100 በላይ ኢትዮጵያዊያን ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጠች

ቻይና ከ100 በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጠች። የትምህርት እድሉ ከ5 አመታት በፊት የተጀመረው የ "ቻይና ኢትዮጵያ ፍሬንድሽፕ ስኮላርሺፕ አካል" ነው።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሲማሩ ለነበሩ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ነው የትምህርት ዕድሉ የተሰጠው። በዚህም መሰረት በመጀመሪያ ዲግሪ ለ80 ተማሪዎች፣ ለ6 ተማሪዎች የሶስተኛ ዲግሪ፣ ለ18 ተማሪዎች የቻይና ቋንቋ፣ ለ12 ተማሪዎች የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተማሪዎች የፕሮጀክት ስኮላርሺፕ እና ለአንድ ተማሪ የጥናት ፈንድ የትምህርት እድል ተሰጥቷቸዋል። በአጠቃላይ የተሰጠው የትምህርት እድል 2 ነጥብ 19 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መሆኑም ተገልጿል። የቻይና መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር በትምህርት ጥናትና ምርምር ዘርፍ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተካሔደው ስነስርዓት…
Read More
ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች

ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች

ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የ2023 ‹‹የዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› አሸነፈች መምህርት፣ ጋዜጠኛና አክቲቪስት መዓዛ መሐመድ የ2023 የ‹‹ዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት (International Women of Courage/IWOC Awards)›› አሸናፊ ሆናለች፡፡  ‹‹ዓለም አቀፍ የጀግና ሴቶች ሽልማት›› በመላው ዓለም ከባድ አደጋዎችንና ፈተናዎችን ተቋቁመው ሰላም፣ ፍትህ፣ ሰብዓዊ መብቶች፣ የፆታ እኩልነት እና የሴቶች ተጠቃሚነት እንዲከበሩና እንዲሰፍኑ ልዩ ጥንካሬ፣ ጀግንነትና የአመራር ጥበብ ላሳዩ ሴቶች የሚበረከት ሽልማት ነው፡፡ ሽልማቱ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚዘጋጅ ሲሆን፣ ዘንድሮ ለ17ኛ ጊዜ የሚካሄድ ይሆናል፡፡ እስካሁን ድረስም ከ80 ሀገራት የተገኙ ከ180 በላይ ጀግና ሴቶችን እውቅና ሰጥቷል፡፡ በዘንድሮው ሽልማት ከአራት አህጉራት የተገኙ 11 ጀግና ሴቶች እና አንድ የሴቶች ቡድን እውቅና ይሰጣቸዋል፡፡    ለሽልማቱ የሚመረጡት ሴቶች…
Read More
ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ

ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ እንድትከፍል ጠየቁ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቻይና 50 ትሪሊዮን ዶላር ካሳ ልትከፍል ይገባል ብለዋል። የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውሀን ቤተ ሙከራ ውስጥ ማምለጡን የሚናገሩት ትራምፕ ቫይረሱ በአሜሪካ ላይ ላደረሰው ጉዳት ቻይና ካሳ እንድትከፍል ጠይቀዋል ሲል ዴይሊ ሜይል ዘግቧል። አሜሪካ በተደጋጋሚ የኮሮና ቫይረስ ከቻይና ቤተ ሙከራ አምልጧል በሚል ስትናገር የሚሰማ ሲሆን ቻይና ግን ይህን ክስ ውድቅ አድርጋለች። የኮረና ቫይረስ በዓለም ላይ ከስድስት ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ሲገድል አሜሪካ፣ ብራዚል እና ሕንድ ብዙ ዜጎቻቸውን በሞት ያጡ ሀገራት ናቸው።
Read More
ሽመልስ አብዲሳ ከብጹአን አባቶች ጋር ስምምነት ላይ ቢደርሱም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተገለጸ

ሽመልስ አብዲሳ ከብጹአን አባቶች ጋር ስምምነት ላይ ቢደርሱም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አባቶች ጋር በወቅታዊ የቤተክርስትያን ጉዳዮች ላይ ተወያይተው ችግሮችን ለመፍታት ቃል የገቡ ቢሆንም አሁንም ችግሮች እንዳልተፈቱ ተነግሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ያቋቋመችው የሕግ ኮሚቴ አባል የሆኑት የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አያሌው ቢታኔ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንቱ በቤተክርስያን ጉዳይ የታሰሩ ሰዎች እስከ ዛሬ ማክሰኞ ድረስ ይፈታሉ ብለው ቃል የገቡ ቢሆንም፣ ሽንገላ የሚመስል ነገር እየተከናወነ ነው ብለዋል፡፡ የኦሮሚያ ክልል መንግሥትና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ሕግን የማስፈጸም ግዴታ እያለባቸው ያለባቸውን ኃላፊነት ባለመወጣታቸው ምክንያት አሁንም በርካታ የሕግ ጥሰቶችና የንብረት ውድመቶች እየደረሱ እንደሆነ ጠበቃው ተናግረዋል፡፡ ትናንት ሰኞ በፍርድ ቤት እግድ የተጣለባቸውና ከቤተክርስትያኗ ቀኖና ውጭ የተሾሙ ግለሰቦች በአሰላ የአቡነ…
Read More