21
Nov
ዋልያዎቹ በዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ በቡርኪና ፋሶ አቻቸው 3 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡ የቡርኪናፋሶን የማሸነፊያ ግቦች ብላቲ ቱሬ በ69 ኛው፣ በርትራንድ ትራኦሬ በ78ኛው እንዲሁም ዳንጎ ኦታትራ 90ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም በ2026 ካናዳ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በጥምረት ለሚያዘጋጁት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ አንድ የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድቡ 1 ነጥብ በመያዝ አምስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ የአለም ዋንጫ የምድቡን ሶስተኛ እና አራተኛ የማጣሪያ ጨዋታዎች ከጊኒ ቢሳኦ እና ጅቡቲ ጋር የሚያደርግ ይሆናል፡፡