USD

የብሪክስ አባል ሀገራት 65 በመቶ ግብይታቸውን ከዶላር ውጭ ማድረጋቸው ተገለጸ

የብሪክስ አባል ሀገራት 65 በመቶ ግብይታቸውን ከዶላር ውጭ ማድረጋቸው ተገለጸ

ኢትዮጵያ አባል በሆነችው ብሪክስ የንግድ ልውውጥ ከዶላር እየራቀ 65 በመቶ በብሔራዊ ገንዘቦች እየተከናወነ ነው ተብሏል። የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እንዳስታወቁት ኢትዮጵያን ጨምሮ አባል የሆኑት የብሪክስ አገራት (ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብፅ፣ ኢንዶኔዢያ፣ ኢራን እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች) በንግድ ልውውጣቸው ከአሜሪካ ዶላር እየራቁ ሲሆን ከ65 በመቶ በላይ የሚሆነው ንግድ አሁን በአባል አገራቱ ብሔራዊ ገንዘቦች እየተከናወነ ነው። ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት በብራዚል በተካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ማጠቃለያ ላይ በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ይህ አዝማሚያ ቡድኑ በፋይናንስ ረገድ ያለውን ነፃነት ለማጠናከር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። ላቭሮቭ አክለውም "BRICS Pay" የተባለ ገለልተኛ የክፍያ ስርዓት ለመመስረት የሚደረጉ ውይይቶች እየተሻሻሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል።…
Read More
አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

አፍሪካ ከዶላር ይልቅ በራሷ ገንዘብ እንድትገበያይ የኬንያ ፕሬዝዳንት ጠየቁ

ኬንያ የአፍሪካ ሀገራት የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ እና አገልግሎት ሲለዋወጡ በራሳቸው ገንዘብ ክፍያ  መፈጸም እንዲጀምሩ ጠይቃለች። ለኢጋድ የመሪዎች ስብሰባ ጅቡቲ ያመሩት የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ አፍሪካ በዶላር ላይ ያላት ጥገኝነት ይብቃ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። “ከጂቡቲ እቃ ገዝተን በዶላር የምንከፍለው ለምንድን ነው? ለምን? ምንም ምክንያት የለም”  ያሉት ፕሬዝዳንት ሩቶ ጂቡቲም ሆነች ኬንያ የእርስ በርስ ግብይት ሲፈጽሙ የአሜሪካ ዶላር መጠቀም አያስፈልጋቸውም ብለዋል። “እኛ የአሜሪካን ዶላር እየተቃወምን አይደለም፤ በነጻነት ግብይት መፈጸም ስለፈለግን እንጂ” ሲሉም ስለ ዶላር አስፈላጊነት ተናግረዋል። እንደ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ዘገባ ፕሬዝዳንቱ ሩቶ አክለውም “ዶላር የሚያስፈልገን ከአሜሪካ ጋር ለምናደርገው ግብይት ብቻ ነው” ሲሉ ገልጸዋል፡፡ በፈረንጆቹ 1993 የተቋቋመው የአፍሪ ኤክዚም ባንክ ግብይቱ…
Read More
ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ኢትዮጵያ ህገ ወጥ የወርቅ እና ጫት ንግድ ፈተና እንደሆነባት ገለጸች

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ እየጎዳው ነው ብለዋል። በዘንድሮው ዓመት የወርቅ እና የጫት ምርት በኮንትሮባንድ ንግድ አማካይነት እየወጣ መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ከአንድ ዓመት በፊት ከአሶሳ 20 ኩንታል ወርቅ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ይላክ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ  ዓመት ግን ሶስት ኩንታል ብቻ መላኩ ለወርቅ ኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋት ማሳያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ከእዚህ ባለፈ የታንታለም ምርት በከፍተኛ ደረጃ ጉጂ ላይ ቢመረትም በህጋዊ መንገድ ወደ ውጪ ተልኮ የውጪ ገቢ ከሚያስገኘው ይልቅ በህገ ወጥ መንገድ ለጎረቤት ሀገራት የሚሸጠው ከፍተኛ ቁጥር እንዳለው አክለው አንስተዋል፡፡ ይህንኑ ከፍተኛ…
Read More