BirrvsUSD

ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

ብሔራዊ ባንክ በልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ አንድ ዶላርን በ107 ነጥብ 9 ብር ሸጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ  ባንክ ለባንኮች ዶላር ለመሸጥ ያወጣው ልዩ ጨረታ ውጤትን ይፋ አድርጓል። በዛሬው እለት በተካሄደው ልዩ ጨረታ 27 ባንኮች የሚፈልጉትን የዶላር መጠን እና የሚገዙበትን ዋጋ አስገብተው ተጫርተዋል። ባንኮቹ ለአንድ የአሜሪካ ዶላር ያቀረቡት አማካይ የመግዣ ዋጋ 107.9 ብር መሆኑን ባንኩ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ጨረታው በነገው እለት ባንኮች በሚያወጡት እለታዊ የውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ለውጥ እንዲመጣ እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብሏል ብሔራዊ  ባንክ። የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ የዶላር ሽያጭ ጨረታው ውጤትን ሲገልጹ ባለፉት ቀናት በባንኮች እና በብላክ ገበያው መካከል ያለው ልዩነት እየጠበበ መሆኑን ተናግረዋል። ይህም የውጭ ምንዛሬ መረጋጋትን ያመጣል ያሉት አቶ ማሞ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሁሉንም የውጭ ምንዛሬ እንቅስቃሴ ወደ ባንክ ስርአት የማስገባት እቅድ…
Read More
ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘቧን በ31 በመቶ አዳከመች

ኢትዮጵያ ከዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ ማድረግ ጀምራለች፡፡ ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰኗን ተከትሎ ባንኮች በዲሱን የምንዛሬ ተመን ዛሬ ተግባራዊ ማድረግ ጀምረዋል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ማሻሻውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫው የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወስንበት የገበያ ሥርዓት መሸጋገሩን አስታውቋል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ባወጣው የውጭ ምንዛሬ ተመን መሰረት አንድ የአሜሪካ ዶላር በ74.7364 ብር እየተገዛ በ76.2311 እየተሸጠ መሆኑን አስታውቋል። ኢትዮጵያ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርአት ተግባራዊነትን ተከትሎ በምንዛሬ ተመን በአንድ ዶላር ላይ በአማካይ የ18 ብር ጭማሪ ታይቷል። በኢትዮጵያ ንግድ…
Read More
መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

መንግስት ብርን የማዳከም ፍላጎት እንደሌለው ገለጸ

ብሔራዊ ባንክ ሪፖርተር ጋዜጣ በሕዳር 23 እትሙ በውጭ ምንዛሬ ተመን ላይ ከፍተኛ ለውጥ ለማድረግ መታቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ሃሰተኛ መሆኑን ገልጿል፡፡ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ በቅርብ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ ለውጥ ለማድረግ ማቀዱን በማስመልከት ያወጣው ዘገባ ፈጽሞ ሐሰተኛና አሳሳች፣ ከጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ያፈነገጠ ድርጊት መሆኑን ባንኩ አስታውቋል፡፡ ባንኩ ይህን አስመልክቶ  ባወጣው መግለጫ የሪፖርተር የአማርኛ ጋዜጣ በህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም እትሙ ብሔራዊ ባንክ ባለፈው ሳምንት የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ለፓርላማ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ከአንድ የፓርላማ አባል ቀረበ ከተባለ አስተያየት ላይ ተነሥቶ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሪ ተመን ላይ…
Read More