መነሻ ገፅ

አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች

አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች

አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና ተመረጠች የኮንፌዴሬሽን ኦፍ አፍሪካ አትሌቲክስ ኮንግረስ በዛምቢያ መዲና ሉሳካ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት የሆነችው አትሌት ደራርቱ ቱሉ የአፍሪካ አትሌቲክስን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንድትመራ ተመርጣለች፡፡ በዚህም ካውንስሉ ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉን የአፍሪካ አትሌቲክስን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንድትመራ በሙሉ ድምጽ መመረጧን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡ የ51 ዓመቷ አትሌት ደራርቱ ሀገሯን እና ራሷን ያስጠራችባቸው በርካታ ሜዳሊያዎችን ያሸነፈች ሲሆን በኦሎምፒክ የ10 ሺህ ሜትር ርቀት ውድድር ታሪክ የወርቅ ሜዳሊያ ያመጣች የመጀመሪያዋ አፍሪካዊ ተብላለች፡፡ አትሌት ደራርቱ ከ2018 ጀምሮ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን ከቀድሞው ፕሬዝዳንት አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ ተረክባ በመምራት ላይ ትገኛለች፡፡ አትሌቷ ባሳካቻቸው በርካታ ውድድሮች ለሌሎች ታዳጊ አትሌቶች…
Read More
ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ“PW ማይኒንግ” ጋር በጋራ ለመስራት ተስማማ

የከፊ ሚኒራልስ ኩባንያ አካል የሆነው ቱሉ ካፒ ጎልድ ማይኒንግ ከእንግሊዙ 'PW ማይኒንግ' ጋር የወርቅ ማዕድን ልማትና በተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል። ስምምነቱ የተፈረመው ከትናንት ሚያዚያ 18/2015 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ በሚገኘው፤ “ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2023” ዓለም አቀፍ የንግድ ተቋማትና ባለሃብቶች ፎረም ጎን ለጎን ነው። በፎረሙ ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ ባለሃብቶች፣ የንግድ ተዋንያን፣ ፖሊሲ አውጪዎች እና ሥራ ፈጣሪዎች እየተሳተፉበት የሚገኝ ሲሆን፤ በመድረኩ የመግባቢያ ሰነድ ስምምነቶች፣ የፓናል ውይይቶች፣ የተመረጡ ኩባንያዎች ጉብኝትና አውደ ርዕይዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኢንቨትመንት ኮሚሽን አዘጋጅነት የሚከናወነው ይህ ፎረም በግብርና፣ ማንፋክቸሪንግ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ ማዕድን እና በቱሪዝም ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በፎረሙ ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨሰትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ፣…
Read More
ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረትን መግለጫ እንደምትቀበል ገለጸች

ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝም ገልጿል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓ ሕብረት ምክር ቤት ከትናንት በስቲያ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ዙሪያ ምላሽ አውጥቷል። ሚኒስቴሩ ምክር ቤቱ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ትግበራ ላይ የተገኙ ውጤቶችን ጨምሮ ለሌሎች ጉዳዮች እውቅና መስጠቱን ገልጿል። ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት ጋር ያላትን ትብብር በአዲስ መልክ እንደገና ለማደስ አበክራ እየሰራች እንደምትገኝና የምክር ቤቱ መግለጫም ይሄንኑ ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን አመልክቷል። ሕብረቱ በዘላቂ ግብርናና የምግብ ዋስትና ላይ ያተኮረውን ዓመታዊ የባለብዙ ዘርፍ የድጋፍ ፕሮግራም በድጋሚ ለመጀመር ያሳየውን ዝግጁነት፣ አበዳሪ አገራት ባቋቋሙት የጋራ ማዕቀፍ ስር የሚከናወነው የኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ የድርድር ሂደት በአፋጣኝ እንዲቋጭ ያቀረበው ጥሪና…
Read More
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በ20 ሺሕ ብር ዋስትና እንዲፈታ ታዘዘ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በ20 ሺሕ ብር ዋስትና እንዲፈታ ታዘዘ

የቀድሞው የ“አል አይን ኒውስ” ጋዜጠኛ እንዲሁም “አራት ኪሎ ሚዲያ” የተሰኘው የዩቲዩብ መገናኛ ብዙሃን አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና የኢትዮ ሰላም የበይነ መረብ ሚዲያ መስራች ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ኹለቱም በ20,000 ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ታዟል፡፡ ውሳኔውን ያስተላለፈው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው። ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ሐሙስ ሚያዚያ 5/2015 ቂሊንጦ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ማክሲኮ ወደሚገኘው ፌደራል ፖሊስ በጸጥታ ኃይሎች መወሰዱን የሚታወስ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፤ ሚያዚያ 4/2015 ምሽት ላይ ባህርዳር ከሚገኘው "ሆምላንድ ሆቴል" በጸጥታ ኃይሎች መወሰዱን መዘገባችን ይታወሳል። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጂ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እያሰረች መሆኑን ጠቅሶ መንግሥት ያሰራቸው  ጋዜጠኞች እንዲፈታ መጠየቁ ይታወሳል።
Read More
የግብጽ ወታደራዊ አታቼ በሱዳን ካርቱም ተገደለ

የግብጽ ወታደራዊ አታቼ በሱዳን ካርቱም ተገደለ

በሱዳን ለ11ኛ ቀን በዘለቀው ጦርነት የሟቾች ቁጥር በየዕለቱ እየጨመረ ይገኛል። ጦርነቱ በሱዳን ብሔራዊ ጦር እና በፈጥኖ ደራሽ ሀይል መካከል ሲሆን አንዱ ባንዱ ላይ ድል መቀዳጀቱ እየተገለጸ ይገኛል። ጦርነቱ እንዲቆም በርካቶች እያሳሰቡ ቢሆንም ተፋላሚ ወገኖች ተኩስ ማቆማቸውን ቢናገሩም ጦርነቱ ግን ቆሞ አያውቅም ተብሏል። የግብጽ መንግሥት እንዳለው በሱዳን ካርቱም የነበራት ወታደራዊ አታቼ መገደሉን አስታውቃለች። ይሁንና ይህ የግብጽ ወታደራዊ አታቼ በማን እንደተገደለ እስካሁን አልተገለጸም። አሜሪካ፣ የአውሮፓ ሀገራት፣ ሳውዲ አረቢያ እና ሌሎችም ሀገራት ዲፕሎማቶቻቸውን ከሱዳን ያስወጡ ሲሆን ቀሪ ዜጎቻቸውን ግን እስካሁን አላስወጡም። በርካታ ዜጎች በካርቱም ጦርነቱ መቀጠሉን ተከትሎ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በኩል አድርገው በመውጣት ላይ እንደሆኑ ተገልጿል። ኢትዮጵያም በመተማ በኩል ከሱዳን የሚመጡ…
Read More
42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

42 ማርኬትስ  ግሩፕ  አስር ሚሊየን ዶላር  ድጋፍ ማግኘቱን ገለፀ

ድርጅቱ ድጋፉን ያገኘው  በግል ባለሀብት ከሚንቀሳቀሰውና  በደቡብ ሰሀራ ሀገራት   በቴክኖሎጂ ላይ ከሚሰራው  ከኮንቨርጀንስ  ፓርተንርስ እና  ከ14  ዓለም ዓቀፍ   የገንዘብ ልማት  ላይ ከሚሰሩ ታዋቂ  የገንዘብ  ተቋማት ነው። በቅርቡ  በዲጂታል   የመሰረተ ልማት ላይ ስራዎች የገንዘብ አቅርቦት ፕሮጅክቱን በ 296 ሚልየን የአሜሪካ ዶላር ያጠናቀቀው  42 ማርኬትስ ግሩፕ ለተጠቃሚዎች ወይም ለንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ልውውጥ  ላይ ከሚሰራው ፊንቴክ ቡድን ወስጥ አንዱ  ቡድን ነው። የ 42 ማርኬትስ ግሩፕ  ስራ አስኪያጅ  አንድሪስ ብሪንክ እንዳሉት  "የተገኘው ገንዘብ ድጋፍ  የዲጂታል ገንዘብ መሰረተልማቱ   ትክክለኛ መተማመኛ እንዲያገኝ ከማድረጉ ባሻገር    ለቀዘቀዘውም  ሆነ እያደገ ለሚመጣ  ገበያ  በጎ የኢንቨስትመንት  ተፅዕኖ እንዲኖረው ያደርጋል" ብለዋል። ከ42 ማርኬትስ ግሩፕ   የበሰሉ ስራዎች ከሚሰሩት  ድርጅቶች መካከል የካፒታል እና  ገበያ አገልግሎቶች …
Read More
በሚዛን አማን ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በሚዛን አማን ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በኢትዮጵያ ሁለት ህጻናት በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው አለፈበመብረቅ አደጋ የአምስት እና የሰባት አመት እድሜ ያላቸዉ የሁለት ታዳጊ ህፃናት ህይወት ማለፉ ተገልጿል። በደቡብ ክልል ቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በመብረቅ አደጋ የሁለት ታዳጊ ህፃናት ህይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡ በከተማው አዲስ ከተማ ቀበሌ ልዩ ስሙ ብርሃን አዲስ ከተማ ሠፈር ከቀኑ 8፡30 የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው መብረቅ የሁለት ህፃናት ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል። አደጋው የደረሰው ሶስት ህጻናት ውሃ ለመቅዳት ወንዝ በሄዱበት ወቅት ዝናብ በመዝነቡ ለመጠለል ዛፍ ስር በሚገኝ ድንጋይ ላይ በተቀመጡበት ወቅት ነው። በዚህ የመብረቅ አደጋ ምክንያትም የሁለቱ ህፃናት ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ በመብረቅ አደጋ ህይወታቸው የሚያልፉ ዜጎች…
Read More
የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ

የኢትዮጵያ የዘጠኝ ወራት የወጪ ንግድ ከአንድ ቢሊዮን ዶላር በላይ ጉድለት አሳየ። የንግድ እና ቀጠናዊ ውህደት ሚንስቴር እንደገለጸው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከወጪ ንግድ 3 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ ነበር። ይሁንና የተገኘው ገቢ ግን በአንድ ቢሊዮን ዶላር ቀንሶ 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር ተገኝቷል ተብሏል። ለገቢው መቀነስ የጸጥታ ችግሮች፣ ህገወጥ ንግድ፣ የዓለም ንግድ መቀዛቀዝ እና የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል። ከተገኘው ገቢ ውስጥም ግብርና የ77 በመቶ ድርሻ ሲያዝ ቀሪው ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና ኤሌክትሪክ ሽያጭ እንደሆኑ ሚንስቴሩ ገልጿል ባለፉት ሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ የቆየችው ኢትዮጵያ የወጪ ንግዷ ተዳክሞ የቆየ ሲሆን በአሜሪካ የተጣለባት ማዕቀብ፣ ህገወጥ የማዕድን ገበያ መስፋፋት ለወጪ ንግዱ ዋነኛ ችግሮች…
Read More
ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለሱዳን 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ እንደምትልክ ገለጸች

ኢትዮጵያ 50 ሺህ ኩንታል ስንዴ ለሱዳን ለመላክ መዘጋጀቷን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ በ”ኢትዮጵያ ኤይድ” በኩል የሚቀርበው ድጋፍ በርካታ መድሃኒቶችንም እንደሚያካትት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል ። ለሱዳን ህዝብ በአሁኑ ወቅት የሚያስፈልገውን ድጋፍ ከማቅረብ ባሻገር ተፋላሚዎቹን ወገኖች ለመሸምገልም ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳላት አንስተዋል። ለሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አልቡርሃን እና ለፈጥኖ ደራሽ ሃይል (አርኤስኤፍ) አዛዡ ጀነራል ሃምዳን ዳጋሎም በድጋሚ ለንግግር ቦታ እንዲሰጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰሜኑ ጦርነት በድርድር እንዲቆም ላደረጉ አካላት እውቅና ሲሰጡ ነው ጥሪውን ያቀረቡት። የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በሽብርተኝነት ከተፈረጀው የኦሮሚያ ነጻ አውጭ ሰራዊት ጋር ድርድር እንደሚደረግ ተናግረዋል ። ድርድሩ በታንዛኒያ የሚካሄድ ሲሆን ኖርዌይ እና ኬንያ አደራዳሪዎች ይሆናሉ ተብሏል።
Read More
ሲፋን ሀሰን የለንደን ሜራቶንን አሸነፈች

ሲፋን ሀሰን የለንደን ሜራቶንን አሸነፈች

የለንደን ማራቶች ከደቂቃዎች በፊት የሁለቱም ጾታ ተዉዳዳሪዎች ፍጻሜውን አግኝቷል። በዚህም ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ እና በዜግነት ሆላንዳዊ የሆነችው ሲፋን ሀሰን አንደኛ ወጥታለች። ለመጀመሪያ ጊዜ በማራቶን ውድድር ላይ የተሳተፈችው ሲፋን ርቀቱን በ2 ሰዓት ከ18 ደቂቃ ከ37 ማይክሮ ሰከንድ አጠናቃለች። ኢትዮጵያዊቷ መገርቱ አለሙ ሁለተኛ ጀፕችርችር ፒሬዝ ከኬንያ ሶስተኛ ወጥተዋል። በርቀቱ ተጠብቃ የነበረችው አልማዝ አያና ውድድሯን በሰባተኝነት አጠናቃለች። በወንዶች የማራቶን ውድድር ደግሞ ኬንያዊው ኬልቪን ኪፕቱም በ2 ሰዓት ከአንድ ደቂቃ ከ25 ማክሮ ሰከንድ አንደኛ ሲሆን ሌላኛው ኬንያዊ ጂዎፍሪ ካምዎሮር ሁለተኛ እንዲሁም ኢትዮጵያዊው ታምራት ቶላ ደግሞ ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል። ልኡል ገብረስላሴ እና ሰይፉ ቱራ ደግሞ አራተኛ እና አምስተኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁ የኢትዮጵያ አትሌቶች ናቸው። በውድድሩ ተጠብቀው የነበሩት…
Read More