Ethiopia

የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የዳታ ማዕከሉ 30 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአፍሪካ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በአዲስ አበባ ከፍቷል። በአፍሪካ ገለልተኛ የመረጃ ማዕከል የሆነዉ ራክሲዮ ግሩፕ በኢትዮጵያ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በ30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ኢንቨስትመንት በመገንባት አስጀምሯል። ኩባንያው የዳታ ማዕከሉን በአዲስ አበባ በአይሲቲ ፓርክ ውስጥ መክፈቱን የገለጸ ሲሆን የዳታ ፍሰትን ሙሉ በሙሉ በአገር ዉስጥ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ድርጅቶች ለኢንተርኔት የሚያወጡትን ወጪ ለመቀነስ ይረዳል ተብላል። በኢትዮጵያ የተከፈተዉ አዲሱ የደረጃ III የመረጃ ማዕከል 800 ራኮች እና እስከ 3MW የአይቲ ሃይል አለዉ ተብሏል። በ2018 የተቋቋመዉ ራክሲዮ በአፍሪካ የመጀመሪያውን የዳታ ማዕከል በኡጋንዳ እንደከፈተ ገልጿል። ኩባንያው ሁለተኛውን የዳታ ማዕከል በኢትዮጵያ ዛሬ ያስጀመረ ሲሆን እስከ ሚቀጥለው ዓመት ድረስም በኮንጎ  ፣…
Read More
ኢትዮጵያ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ኢትዮጵያ ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ አገኘች

ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር መገኘቱ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በአራት ዓመታት ውስጥ ወደ ውጪ ሀገራት ከተላኩ ምርቶች አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር መገኘቱን የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አስታወቀ። በአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ በዓመት 17 ሚሊዮን ዶላር ገቢ የሚያስገኙ የተለያዩ የፕላስቲክ ቱቦዎችን የሚያመርት ፋብሪካ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል። የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አክሊሉ ታደሠ፤ ኮርፖሬሽኑ ከሚያስተዳድራቸው 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተለያዩ ምርቶች ለውጭ ገበያ እየቀረቡ መሆኑን ተናግረዋል። ኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ለተለያዩ ሀገራት ገበያ ከሚያቀርቧቸው ምርቶች በአራት ዓመታት ውስጥ አንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ሀላፊው ተናግረዋል፡፡ ከውጭ ሀገራት ይገቡ የመበሩ ምርቶችን በሀገር…
Read More
የኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሺህ በላይ ሃኪሞችን ለመቅጠር ቢፈልግም ተቀጣሪ ማጣቱን ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሺህ በላይ ሃኪሞችን ለመቅጠር ቢፈልግም ተቀጣሪ ማጣቱን ገለጸ

የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ባለፈዉ ዓመት ሰኔ ወር 2015 ዓ.ም ማስታወቂያ ቢያወጣም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ በጀቱን ወደ ሌላ ዘረፍ ማዛወሩን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታዉቋል፡፡ የቢሮዉ ምክትል ሃላፊ ዶ/ር ጉሻ በለኮ በሰኔ 2015 ላይ 1ሺህ 1መቶ ሀኪሞችን ለመቅጠር ማስታወቂያ የወጣ ቢሆንም ተቀጣሪዎችን ባለማግኘቱ ቢሮዉ በጀቱን ለሌላ ጉዳይ ማዋሉን ለጣቢያችን ተናግረዋል፡፡ ለ 2 ወራት ያክል ማስታወቂያዉን ክፍት ባደርግም ገበያ ላይ ተቀጣሪዎችን አላገኘሁም ብሏል ቢሮዉ፡፡ በየአንዳንዱ ጤና ተቋም ሀኪሞች መኖር ስላለባቸዉ ያንን ለማሟላት ማስታወቂያ ብናወጣም ሀኪሞችን ባለማግኘታችን በምትኩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎችን፣ አዋላጆችን እና ነርሶችን ለመቅጠር ተገደናል ነዉ ያሉት፡፡ ከዚህ በፊት ለመላዉ ኦሮሚያ አገልግሎት የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር 72ሺህ ነበር ያሉት…
Read More
ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ ረጅም ዓመት ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን ልታግድ መሆኗን ገለጸች

በአዲስ አበባ ከፍተኛ ጭስ የሚለቅ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች አስቀድመው መፍትሄ እንዲያዘጋጁ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ ተሸከርካሪዎች የሚለቁትን ጭስ የሚለካ መሳሪያ እና ጥራት ማስጠበቂያ ወይም ስታንዳርድ በመዘጋጀት ላይ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ድዳ ድሪባ እንደተናገሩት የመኪና ጭስ ስታንዳርድ እየተዘጋጀ ነው የተባለ ሲሆን እያንዳንዱ መኪና የሚያስወጣው ጪስ ይለካል ተብሏል። መኪናው ከተቀመጠው መለኪያ በላይ ጪስ የሚያመነጭ ከሆነ አገልግሎት እንዳይሰጥ ይደረጋል ብለዋል። አብዛኛውን ጊዜ ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ ተሽከርካሪዎች ከተመረቱ 23 ዓመትና ከዚያ በላይ ያገለገሉ ናቸው ያሉት ኃላፊው፤ ስለዚህ አሮጌ መኪና ያላቸው አሽከርካሪዎች ከአሁኑ መፍትሄ ሊያዘጋጁ ይገባል ብለዋል። በመዲናዋ አሮጌና ከፍተኛ ጭስ የሚለቁ በርካታ መኪኖች መኖራቸውን…
Read More
ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል ኢስቴት 754 መኖሪያ ቤቶችን አስመረቀ

ኖህ ሪል እስቴት አስረኛ ዓመቱን 754 አዳዲስ መኖሪያ ቤቶችን በማስረከብ አክብሯል ኖህ ሪል ስቴት ኃ/የተ/የግ/ማህበር 10ኛ አመት የምስረታ በአሉን  754 አዳዲስ የመኖሪያ ቤቶችን ገንብቶ በማስረከብ አክብሯል። በኢትዮጵያ የከተማ ልማት ከፍተኛ እድገት አበርክቶ ያለው ኖህ ሪል ኢስቴት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ደንበኞቹና የሚዲያ አባላት ጋር አክብሯል። ኖህ ሪል እስቴት ባለፉት አስርት አመታት 8,000 በላይ ለሆኑ ቤተሰቦች በከፍተኛ ጥራት የተገነቡ ቤቶችን በታማኝነት፣ በሰዐቱ እና በቃሉ መሰረት አስረክቧል። ይህ ጉዞ ኩባንያውን በኢትዮጵያ የቤቶች ልማት ዘርፍ ቁልፍ ተዋናይ ሆኖ እንዲቀጥል አስችሎታል።  ለአገራዊ የልማት ግቦች ስኬትም ትልቅ አስተዋፅዖ እያደረገ ይገኛል። የኖህ ሪል ኢስቴት ዋና ስራ አስፈፃሚ ንፁህ አዉግቸዉ “በዛሬው ዕለት በኖህ ግሪን ፓርክ ሳይት አዲስ የተገነባውን …
Read More
አቦል ቴሌቪዥን “ዳግማዊ” እና “ቁጭት” የተሰኙ አዲስ ተከታታይ ድራማዎችን ማስተላለፍ ሊጀምር ነው

አቦል ቴሌቪዥን “ዳግማዊ” እና “ቁጭት” የተሰኙ አዲስ ተከታታይ ድራማዎችን ማስተላለፍ ሊጀምር ነው

አቦል ቴሌቪዥን ከሰኞ ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁለት አዳዲስ “ሀገርኛ” ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማዎችን ለተመልካቾቹ ላቀርብ ነው ብሏል፡፡ ለተመልካቾች የሚቀርቡት “ቁጭት” የተሰኘው ረጅምና ወጥ ሀገርኛ ተከታታይ ቴሌኖቬላ እና “ዳግማዊ” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው ድራማ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ይዘቶች አቦል ቴሌቪዥን ለደንበኞቹ ምርጥ ወጥ ሀገርኛ ይዘቶችን ለማቅረብ የወጠነውን ጅምር በተግባር የሚያረጋግጡና ቻናሉ የላቁ መዝናኛዎችን ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ናቸው። “ቁጭት” የተሰኘው ሀገርኛ ቴሌኖቬላ ታሪኩ የሚያጠነጥነው በሕይወት ጥቂት ወራት ብቻ እንደሚቀረው ከተነገረው በኋላ የናፈቀውን ልጁን ዮናስን ለማግኘት ፍለጋ በጀመረ አባት ነው፡፡ ድርጊቱ በተስፋ ማጣት እና በድህነት ውስጥ ያለን የሕይወት ውጣውረድም የሚያስቃኝ ሲሆን ዮናስ የአባቱን ህልውና እና ባለጸጋነት ታሪክ ሳያውቅ ሕይወቱ…
Read More
ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ግጭት ውስጥ መግባቷን አመነች

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚንስቴር በወቅታዊ የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥታል። የሚንስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በተለያዩ የዲፕሎማሲ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ ማብራሪያ ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል ከሰሞኑ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ልማት ባንክ መክፈል ያለባትን ብድር ከመክፈል ጋር በተያያዘ አለመግባባት ተፈጥሯል የሚለው ጉዳይ ነው። አለመግባባቱ በኢትዮጵያ ገንዘብ ሚንስቴር እና በአዲስ አበባ ካለው የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያ ቢሮ ጋር መካከል ነው የተባለ ሲሆን በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያትም ባንኩ ቢሮውን ዘግቶ ሆዷል የሚል ነበር። በሁለቱ አካላት መካከል የተፈጠረው ግጭት ምንድን ነው? ባንኩስ የኢትዮጵያ ቢሮውን ዘግቶ ወጥቷል? በሚል ለአምባሳደር መለስ ዓለም ጥያቄ ከጋዜጠኞች ቀርቦላቸው ነበር። አምባሳደር መለስ በምላሻቸውም "ከአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ…
Read More
አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያቋረጠችውን እርዳታ ልትጀምር መሆኗን ገለጸች

የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ከመጪው ወር ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ የምግብ እርዳታ አጀምራለሁ ብሏል፡፡ የአሜሪካ  መንግስት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) ካሳለፍነው ሰኔ ወር ጀምሮ በምግብ እርዳታ ስርቆት ምክንያት እርዳታ መስጠቱን ማቆሙ ይታወሳል፡፡ በለጋሾች የተገዛ የምግብ እርዳታ ለገበያ መቅረቡና ወደ ውጪ አገራት ጭምር መላኩን የጠቀሰው የተራድኦ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የእርዳታ ስርጭቱን በተመለከተ ተከታታይ ውይይት ማድረጉን ገልጿል። በዚህም ባለፈው ወር በሀገሪቱ ለሚገኙ ስደተኞች የምግብ እርዳታ ማቅረብ የጀመረ ሲሆን ከመጪው ወር ጀምሮ ደግሞ በመላው ኢትዮጵያ ድጋፍ ለሚሹ ወገኖች እርዳታ ማቅረብ እንደሚጀምር ገልጿል። ኢትዮጵያ የምግብ ድጋፍ ስርጭት ስርአቷን በመሰረታዊነት የሚያስተካክል ስራ መከወኗንና ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታው ለተገቢው አካል መድረሱን እንዲከታተሉ መስማማቷን ድርጅቱ አስታውቋል። ለጋሽ…
Read More
ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ስድስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ተገለጸ

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን እንደሚመድብ ገልጿል፡፡ ይሁንና ስድስት የመንግስት ዩንቨርሲቲዎች የሬሚዲያል ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ አስታውቋል፡፡ የሬሚዲያል ተማሪዎችን ከማይቀበሉ ዩንቨርሲቲዎች መካከልም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዪኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እነዚህ ዩንቨርሲቲዎች ለምን የሬሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎችን እንደማይቀበሉ ምክንያታቸውን አልጠቀሰም፡፡ በ2015 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺሕ 099 ተማሪዎች ውስጥ፤ 817 ሺሕ 838 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በታች የሆነ ውጤት ማምጣታቸው ይታወሳል፡፡ የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በሰጡት መግለጫ ከአጠቃላይ 845 ሺሕ 099 ተፈታኞች ውስጥ…
Read More
የሱዳን ጦር አዛዥ ጀነራል አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

የሱዳን ጦር አዛዥ ጀነራል አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

የሱዳን ሉአላዊ ምክርቤት ፕሬዝዳንትና የሀገሪቱ ጦር አዛዥ ጀነራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን ለይፋዊ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ጀነራል አልቡርሃን በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታና በሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ይወያያሉ ተብሏል። ሰባተኛ ወሩን የያዘው የሱዳን ጦር እና የፈጥኖ ደራሽ ሃይሉ ጦርነት ከ9 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ሰዎችን ያፈናቀለው ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲቆም የሚደረገው ጥረትም ቀጥሏል። ሁለቱ ሃይሎች በሪያድ በተደጋጋሚ ለድርድር ቢቀመጡም እስካሁን ከስምምነት ላይ አልደረሱም። በአዲስ አበባም በቅርቡ በሱዳን የሽግግር መንግስት ለማቋቋም ያለመና ከ80 በላይ የሀገሪቱ የፖለቲካና ሲቪል ድርጅቶች የተሳተፉበት ምክክር መደረጉ አይዘነጋም። በካርቱም የሚገኘው ኤምባሲዋ በአየር የተደበደበባት ኢትዮጵያ ከምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት…
Read More