Valenciamarathon2023

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

የቫሌንሲያ ማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ

በስፔኗ ቫሌንሲያ የተካሄደው የማራቶን ውድድር በኢትዮጵያዊያን የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ የሚነግሱባት የስፔኗ ቫሌንሲያ ዛሬም ኢትዮጵያዊያን ተመሳሳይ ድሎችን አግኝተውባታል፡፡ በዚው ውድድር በሁለቱም ጾታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በአንደኝነት አጠናቀዋል፡፡ በሴቶች የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊያን ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ በበላይነት ሲያሸንፉ አትሌት ውርቅነሸ ደገፈ፣ አልማዝ አያና እና ህይወት ገብረኪዳን ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ጠናቀዋል፡፡ በዚህ የወንዶች የማራቶን ውድድር ላይ አትሌት ሲሳይ ለማ አንደኛ፣ ኬንያዊው አትሌት አሌክሳንደር ሙቲሶ ሁለተኛ እንዲሁም ዳዊት ወልዴ እና ቀነኒሳ በቀለ ሶተኛ እና አራተኛ ሆነው አጠናቀዋል፡፡ አትሌት ሲሳይ ለማ ርቀቱን 2:01:48 በሆነ ሰአት ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን የቦታውን ክብረወሰን ማሻሻል ሲችል ተጠብቆ የነበረው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ አራተኛ ሆኖ ማጠናቀቅ ችሏል፡፡…
Read More
አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ ገለጸ

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በሚካሄደው የቫሌንሺያ ማራቶን እንደሚሳተፍ አስታውቋል፡፡ አትሌቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው "ከብዙ ጊዜ ጉዳት በኋላ በቫሌንሺያ ማራቶን እሳተፋለሁ" ብሏል። "ከብዙ ጉዳት በኋላ ወደ ውድድር በመመለሴ ደስተኛ ነኝ" ያለው አትሌት ቀነኒሳ አኤኤንቲኤ የተሰኘው ኩባንያ ስፖንሰሬ ነው፣ ላደረገልኝ ድጋፍ አመሰግናለሁ " ሲልም ገልጿል። ውድድሩ የፊታችን ሕዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም በስፔኗ ቫሌንሲያ እንደሚካሄድ ተገልጿል። አትሌት ቀነኒሳ በአምስት እና አስር ሺህ ውድድሮች ላይ ለዓመታት ሳይረታ የቆየ ውጤታማ አትሌት ሆኖ ቆይቷል። በሁለቱም ርቀቶች የዓለም ሪከርዶችን ለ16 ዓመታት ይዞ የቆየው አትሌት ቀነኒሳ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ፊቱን ወደ ማራቶን ውድድር አዙሯል። የማራቶን ውድድርን ከሁለት ሰዓት በታች ይገባል ተብሎ ከሚጠበቁት…
Read More