Ethiopia

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ጥምረትን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተገለጸ

ከ24 ዓመት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን የኢኮኖሚ ትስስር ለማሳለጥ የተቋቋመው የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ ጥምረት በየጊዜው አዳዲስ አባላትን በመሳብ ላይ ይገኛል። ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ከአንድ ዓመት በፊት ይህን ጥምረት ለመቀላቀል በይፋ መጠየቋ ይታወሳል። ጥምረቱም የመቋዲሾን ጥያቄ ለመመለስ ባለሙያዎቹን አሰማርቶ የተለያዩ ግምገማዎችን ሲያደርግ ቆይቶ ሶማሊያን ስምንተኛዋ አባል ሀገር አድርጎ እንደሚቀበል አስታውቋል። ዋና መቀመጫውን አሩሻ ታንዛኒያ ያደረገው ይህ የኢኮኖሚ ጥምረት በሚቀጥለው ሳምንት በሚያደርገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ሶማሊያን በይፋ በአባልነት እንደሚቀበል ገልጿል። የጥምረቱ ዋና ጸሀፊ ፒተር ማቱኪ በሞሮኮ ማራካሽ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ እንዳሉት "ሶማሊያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አባል ትሆናለች" ብለዋል። ዋና ጸሀፊው አክለውም "የጥምረቱ ቀጣይ አባል ሀገር ኢትዮጵያ ልትሆን ትችላለች፣ ኢትዮጵያ…
Read More
የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

የማራቶን ባለ ሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ሽልማት የመጨረሻውን ዙር ተቀላቀለች

አትሌት ትግስት አሰፋ ለአለም አትሌቲክስ በዓለም ምርጥ የዓመቱ አትሌቶች ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱ ምርጥ 10 የዓለም አትሌቶች መካከል አንዷነበረች። የዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በ2023 ዓመት በተካሄዱ የተለያዩ ውድድሮች ላይ ስኬታማ የሆኑ አትሌቶችን ዝርዝር ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በመጀመሪያው ዙር 11 ምርጥ የዓለማችን አትሌቶች ዝረዝር ውስጥም የ5 ሺህ ሜትር ባለ ሪከርዷ ጉዳፍ ጸጋዬ እና የማራቶን ባለሪከርዷ አትሌት ትግስት አሰፋ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱ አትሌቶች ነበሩ። ዎርልድ አትሌቲክስ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት በውድድሩ ለመጨረሻ ዙር ያለፉ አትሌቶችን ዝርዝር አውጥቷል። በዚህም የማራቶን ባለሪከርዷ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ ለመጨረሻ ዙር ውድድር ከቀረቡ አትሌቶች መካከል እንዷ ሆናለች። ከአትሌት ትግስት አሰፋ በተጨማሪ ኬንያዊቷ አትሌት ፋይዝ ኪፕዬጎን፣ ጃማይካዊቷ ሸሪካ ጃክሰን፣ የኔዘርላንዷ…
Read More
የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና ጃል መሮ ፊት ለፊት ተገናኙ

የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ አመራር እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መሪው ጃል መሮ ፊት ለፊት መገናኘታቸው ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂ ቡድን መካከል በታንዛኒያ የሁለተኛ ዙር የሰላም ንግግር መጀመራቸው ተሰምቷል። ቢቢሲ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ባወጣው ዘገባ የሰላም ንግግሩ ጥቂት ቀናትን እንዳስቆጠረና ከሁለቱም ወገኖች የተወጣጡ የጦር አባላት ተወካዮች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ከዚህ ቀደም ራስ ገዝ ግዛት በሆነችው ዛንዚባር የተካሄደውን ድርድር የምሥራቅ አፍሪካ በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ)፣ አሜሪካ፣ ኖርዌይ እና ኬንያ አስተባባሪ እና አሸማጋይ ሚና መውሰዳቸው ይታወሳል። አሁን የተጀመረውን ንግግር ማን እንደሚያደራድር ግልጽ ባይሆንም፣ ኢጋድ ከዚህ ቀደም የነበረውን ሚና ሳያስቀጥል እንዳልቀረ ተጠቅሷል። ከዚህ በተጨማሪ አዲስ…
Read More
አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

አሰልጣኝ ገብረመድህን ኃይሌ ዋልያዎቹን በአሰልጣኝነት ተረከቡ

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሐየራዊ ቡድን አሰልጣን የነበሩት ገብረመድህን ሀይሌ በድጋሚ ዋልያዎቹን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ መድን እግር ኳ ክለብን በማሰልጠን ላይ የነበሩት አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ በአንድ ዓመት ውል ብሔራዊ ቡድኑን እንዲያሰለጥኑ ተመርጠዋል፡፡ አሰልጣኙ የብሔራዊ ቡድን ስራቸውን ከኢትዮጵያ መድን እግር ኳስ ክለብ ጋር ደርበው እንዲያካሂዱ ከፌዴሬሽኑ ጋር እንደተስማሙም ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ የሚያደርጋቸውን ሁለት ቀጣይ የሜዳው ጨዋታዎችን ወደ ሞሮኮ ተጉዘው ያካሂዳሉም ተብሏል። የመጀመርያው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ከሴራሊዮን ኅዳር 5 እንዲሁም ሁለተኛው ጨዋታ ከቡርኪና ፋሶ ጋር ኅዳር 11 የሚደረግ ሲሆን ሁለቱም ጨዋታዎች በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ይደረጋሉ፡፡ ብሄራዊ ቡድኑን በኢንተርናሽናል ውድድር ተፎካካሪ ማድረግ የሚጠብቅባቸው አሰልጣኝ ገብረመድህን…
Read More
የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

የጸጋ ተስፋዎች እና በህይወት የመኖር ትግል

ጸጋ ትባላለች በትግራይ ክልል ደንጎላት በተባለ አካባቢ የተወለደች ሲሆን እድገቷም ሆነ የትዳር ሕይወቷን በዚያው ያደረገች ወጣት እናት ናት። ጸጋ ወደ ትዳር ስትገባ የ16 ዓመት ታዳጊ ነበረች በወቅቱ በቤተሰብ ስምምነት በተፈጸመው በዚህ ትዳር 2 ሴት እና 2 ወንድ በአጣቃላይ 4 ልጆችን አፍርተውበታል። በወቅቱ በነበሩበት አካባቢ በቆሎ በማምረት እና በመሸጥ ከባለቤቷ ጋር ጥሩ ኑሮ ይኖሩ የነበሩ ሰዎችም ነበሩ። ነገር ግን ይህ ጥሩ የሚባለው ኑሮ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ የተገላቢጦች እየሆነ መጣ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተፈጠረው ጦርነት ነገሮች መስመራቸውን እየለቀቁ መጡ... በወቅቱ የንግድ እንቅስቃሴዎች እየቀነሱ መምጣታቸው መሠረታዊ የሚባሉ ነገሮች በተለይም ምግብ ነክ ሸቀጦች ዋጋቸው የማይቀመስ ሆነ እንደ ቡና፣ ጨው፣ ስኳር እና መሰል ነገሮችን ማግኘት…
Read More
ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት ማምጠቂያ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ ETRSS-02 የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሶስተኛዋን የመሬት ምልከታ ሳተላይት በወራት ውስጥ እንደምትመጥቅ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም መራዘሙ ተገልጿል፡፡ የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ከሶስት ወራት በፊት በሰጠው መግለጫ በቅርቡ ሶስተኛዋን ሳተላይት አመጥቃለሁ ሲል ገልጾ ነበር፡፡ ይሁንና ETRSS-02 የተሰኘችው ሳተላይት በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደምትመጥቅ አስታውቋል፡፡ ከዚህ በፊት በቻይና አጋዥነት ወደ ሕዋ የመጠቁት ሳተላይቶች የተቀመጠላቸውን የአገልግሎት ጊዜ በመጨረስ ተልዕኳቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል። የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አብዲሳ ይልማ፤ ሶስተኛውን ሳተላይት መምጠቅን በተመለከተ መንግስት የፋይናንስና የኢኮኖሚ አዋጪነት ጥናት ማድረጉን ገልጸዋል። ጥናቱ ከዚህ በፊት ወደ ሕዋ ከመጠቁት ሳተላይቶች ተሞክሮ በመውሰድ የቀጣዩን ሳተላይት መረጃ ከመጠቀም አልፎ ሌሎች ተልዕኮዎችን በግልጽ ማስቀመጡንም አመልክተዋል። የሳተላይቱን ጨረታ…
Read More
የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ሞላው

የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ አንድ ዓመት ሞላው

ህወሀት የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝን ማጥቃቱን ተከትሎ ነበር በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የተቀሰቀሰው። ለሁለት ዓመት የዘለቀው ይህ ጦርነት 800 ሺህ ገደማ ኢትዮጵያዊያን ህይወታቸውን እንዲያጡ ሲያደርግ 26 ቢሊዮን ዶላር የኢኮኖሚ ኪሳራም አድርሷል። ለዚህ ጦርነት መቆም ምክንያት የሆነው የሰላም ስምምነት ከአንድ ዓመት በፊት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተፈርሟል። የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም ስለ ስምምነቱ እና ሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት በፌደራል መንግሥት እና ትግራይ ሀይሎች መካከል የተካሄደው የሰላም ስምምነት ለኢትዮጵያ ምን ጥቅም አስገኘ? በሚል ከጋዜጠኞች ጥያቄ ለቃል አቀባዩ ተነስቶላቸዋል። አምባሳደር መለስ በምላሻቸውም " ስምምነቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል ጦርነት እንዲቆም ከማድረግ በተጨማሪ ኢትዮጵያ ላይ…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ የቴሌኮም አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ የቴሌኮም አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ

ሳፋሪኮም በትግራይ ክልል የኔትወርክ እና መሠረት ልማት ዝርጋታ በሚቀጥሉት ሳምንታት እንደሚጀምር ገልጿል ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ የገባው ሳፋሪኮም ከትግራይ ክልል ውጪ በመላው አገሪቱ የቴሌኮም አገልግሎቱን ለደንበኞቹ ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡ በትግራይ ክልል በነበረው ጦርነት ምክንያት የቴሌኮም አገልገሎቱን ማቅረብ ያልቻለው ይህ ኩባንያ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ አገልግሎት እጀምራለሁ ብሏል፡፡ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሔለፑት ወደ ትግራይ ክልል አምርተው ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳድር አመራሮች ጋር መምከራቸውን ድርጅቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል፡፡ በሚቀጥሉት ሳምንታት በትግራይ ክልል የኔትወርክ እና የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ለማካሄድ በሚያስችለውን ውይይት ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር አድርጓል፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው እና ሌሎች ሰራተኞች ወደ መቀሌ ከተማ ተጉዘው ከጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው…
Read More
በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ የአህያ ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ መሆኑ ተገለጸ

በአህያ ደህንነት ዙሪያ የሚሰራው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ድርጅት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ የአህያ ስጋን ወደ ውጪ ሀገራት መላክ የተጀመረ ሲሆን ዓላማውም የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት እንደሆነ ይገለጻል፡፡ በዚህ የአህያ እርድ3 እና ንግድ ምክንያት የአህያ ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱን እና ይህም እንዳሳሰበው ብሩክ ኢትዮጵያ የተሰኘ የአህያ መብት ተሟጋች ድርጅት አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ አህያ እንዲታረድ እና ስጋና ቆዳው ለውጭ ገበያ እንዲቀርብ መደረጉ እንደ አገር የአህያ ቁጥር እየተመናመነ እንዲመጣ ማድረጉን የብሩክ ኢትዮጵያ ድርጅት አማካሪ ይልማ አበበ ለመናኃሪያ ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡ በኢትጵያ የአህያ እርድ በቻይና ባለሃብቶች በመስፋፋቱ ለአገር የውጭ ምንዛሪን ቢያስገኝም፤ እንደ አገር የአህያ መኖር ከጊዜ ወደ ጊዜ አሳሳቢ ደረጃ ላይ…
Read More
አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

አየርላንድ ለኢትዮጵያ የምግብ ደህንነት 8.4 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ተስማማች

የገንዘብ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር እና የአየርላንድ መንግሥት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የ8 ሚሊየን 400 ሺሕ ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የፈረሙት የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ እና የአየርላንድ የዓለም አቀፍ ልማትና ዳያስፖራ ሚኒስትር ዴዔታ ሾን ፍሌሚንግ ናቸው፡፡ የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ ሦስት ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ የመጀመሪያው 5 ሚሊየን ዩሮ ለሴፍቲ ኔት ፕሮግራም እንዲሁም 3 ሚሊየን ዩሮ በጤና ላይ ያተኮሩ ዘላቂ የልማት ግቦችን ለመደገፍ እንደሚውል ተገልጽልል። እንዲሁም 400 ሺሕ ዩሮ ደግሞ ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሐ-ግብር ድጋፍ እንደሚውል በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ ከፊርማ ሥነ- ሥርዓቱ በኋላ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ባደረጉት ንግግር፤ አየር ላንድ ለኢትዮጵያን የልማት ሥራዎች ቀጣይነት እያደረገችው ላለው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ሦስቱም ስምምነቶች በመንግሥት…
Read More