Dam

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More