Dam

ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ታላቁ የህዳሴ ግድብ በቀጣዮቹ ስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቃል ተባለ

ከ15 ዓመት በፊት በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ግንባታው የተጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በያዝነው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል፡፡ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት ላይ ናቸው። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ለተነሳው ጥያቄ ምላሽ በሰጡበት ውቅት እንዳሉት ህዳሴ ግድብን ከ6 ወር በኋላ እንመርቃለን ብለዋል፡፡ መንግስት ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ መንግስት ጋር በተለይም ከደህንነት መስሪያ ቤት ጋር ህዳሴን በተመለከተ ውይይት አድርገናል የተለያዩ ሃሳቦችም በህዳሴ ግድብ ዙሪያ አቅርበናል ብለዋል፡፡ መንግስት በህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ከግብፅ ጋር ለመነጋገርና ለመወያየት ዝግጁ ነው ሲሉ ጠቅሰዋል:: የግድቡ ግንባታ ከተጀመረ 15 ዓመታት ሊሞሉት አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።…
Read More
ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ግድቦችን በመገንባት ላይ መሆኗን ገለጸች

የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር እንደገለጸው ኢትዮጵያ 28 የመስኖ ፕሮጀክቶችን በመገንባት ላይ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በግንባታ ላይ ካሉት የመስኖ ግድቦች ውስጥም 13ቱን በተያዘው የ2016 ዓመት በከፊል ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በዚህ ዓመት እንዲጠናቀቁ በሚል እየተገነቡ ላሉ ግድቦችም 8 ነጥብ 03 ቢሊዮን ብር መመደቡ ተመልክቷል፡፡ የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጀት እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በሀገሪቱ 28 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመከናወን ላይ ነው፡፡ 13 የመስኖ ፕሮጀክቶች በከፊል ሲጠናቀቁ 2 ሺህ 450 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ እንደሆኑም ሃለፊው ተናግረዋል፡፡ እየተገነቡ ካሉት ግድቦች በተጨማሪም 27 አዲስ የመስኖ ግድቦችን ለመገንባት የጥናትና ዲዛይን…
Read More