Ethiopia

በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የሚፈጸሙ ግድያዎች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

በአማራ ክልል በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የሚፈጸሙ ግድያዎች መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ገለጸ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል በቀጠለው ጦርነት ዙሪያ ያደረገውን የምርመራ ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ኮሚሽኑ እንዳለው በአማራ ክልል ባለው ጦርነት የደረሱ ጉዳቶችን ለመመርመር መንግሥታዊ ኃላፊዎችን፣ በግጭቱ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎችን፣ የዐይን ምስክሮችን፣ ተጎጂዎችንና የተጎጂዎች ቤተሰቦችን በማነጋገር መረጃዎችንና ማስረጃዎችን ማሰባባቡን ገልጿል፡፡ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ በአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በመንግስት የጸጽታ ሀይሎች እና በተለምዶ ፋኖ በመባል ከሚታወቀው አካል ጋር ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ ይህ ጦርነት በአንዳንድ አካባቢዎች በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር/ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው ያለ ሲሆን በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡ በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ መጥተህ ብላ ከተማ፣…
Read More
በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

በአማራ እና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ 300 ዜጎች በታጣቂዎች ተገደሉ

የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የሚዋሰኑበት የሰሜን ሸዋ ዞን ስራ የሚገኙ ወረዳዎች በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ጥቃት እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ ደራ የተሰኘው ወረዳ ደግሞ በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ጥቃት የሚደርስበት አካባቢ ሲሆን በሶስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ 300 ንጹሃን ዜጎች በታጣቂዎች መገደላቸው ተገልጿል፡፡ ኦነግ ሸኔ ከሶስት ዓመት በፊት  በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት ተፈርጆ መንግስት ይህን የሽብር ቡድን ለማጥፋት እርምጃ እየወሰድኩ ነው ቢልም ቡድኑ ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል፡፡ አንድ ሥማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የደራ ወረዳ ነዋሪ ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንዳሉት "በሦስት ሳምንታ ውስጥ ከ300 በላይ ንጹሐን በሸኔ ታጣቂዎች ተገድለዋል።" ያሉ ሲሆን፤ ይህ እርሳቸው ያላቸው ትክክለኛ መረጃ እንደሆነ በመግለጽ፤ የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችል እርግጠኛ መሆናቸውን…
Read More
በኦሮሚያ ክልል በጉንፋን መሳይ ወረርሽኝ በሽታ የ78 ሰዎች ህይወት አለፈ

በኦሮሚያ ክልል በጉንፋን መሳይ ወረርሽኝ በሽታ የ78 ሰዎች ህይወት አለፈ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ በተቀሰቀሰ ጉንፋን መሳይ ወረርሽኝ በአንድ ቀበሌ ብቻ የ78 ሰዎች ህይወት አልፏል። የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ በበኩሉ የወረርሽኙን መከሰት አረጋግጦ አፋጣን ምላሽ ለመስጠት እየጣረ መሆኑን አስታውቋል። ወረርሽኙ ከምዕራብ ወለጋ በተጨማሪ ቄለም ወለጋ ውስጥ መከሰቱንም ዶይቼ ቬለ ከነዋሪዎች አረጋግዐጫለሁ ብሏል፡፡ በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ወረዳ የሌሊስቱ ሎጲ ቀበሌ ነዋሪ እንደሚሉት በአካባቢው መቋጫ የታጣለት የጸጥታ ችግር ነዋሪውን ለረሃብ እና የወረርሽኝ በሽታ አጋልጦ በርካቶችን ለህልፈት እየዳረገ ነው። “አሁን እኛ ጋ ከፍተኛ የምግብ እጦት ይስተዋላል፡፡ ይህም መነሻው ድርቅ አጋጥሞን አሊያም በፋጣሪ ቁጣ ሳይሆን ሰው በፈጠረው ግጭት ወጥቶ ማረስ አይደለም ወጥቶ መግባቱ ፈተና ሆኖ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡ በኦሮሚያ ክልል…
Read More
ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ሙስና ፈጽመዋል የተባሉ 42 ተጠርጣሪዎች ታሰሩ

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ህዝብን ከማማረራቸው ባለፈ ለውጭ ሀገራት ዜጎች ፓስፖርት ሲሰጡ ነበርም ተብሏል፡፡ በሙስና ተጠርጥረው በፖሊስ ከታሰሩ ሰዎች መካከል የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዳይሬክተሩ ይገኙበታል፡፡ 42 የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኞች ባሳለፍነው ሰኞ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ ናቸው ተብሏል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ ፓስፖርት ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን መንገላታታቸውን ተከትሎ የተቋሙን አመራሮች ከስልጣን አግደው ነበር፡፡ ሰላማዊት ዳዊት ደግሞ…
Read More
ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ኢትዮጵያ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ በጎረቤት ሀገራት ውድቅ ተደረገ

ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስት አብይ አህመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ የህዝቧን የመልማት ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት የባህር በር ያስፈልጋታል ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ኢትዮጵያ የጣላቁ ህዳሴ ግድብን ስትገነባ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ሀገራት ጠይቀዋል፣ እኛም የባህር በር እንዲኖረን መጠየቅ አለብን ሲሉም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል ያበሉ እንጂ ስለየትኛው የባህር በር ግን ስም አልጠቀሱም ነበር፡፡ ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆኑት እና የባህር በር ያላቸው ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማሊያ ሲሆኑ ሶስቱም ሀገራት የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ ውድቅ አድርገዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ አስቀድሞ መግለጫ ያወጣው የኤርትራ መንግስት ሲሆን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣው መግለጫ ሀገሪቱ ሀብቷን ለማንም አሳልፋ እንደማትሰጥ፣ እስካሁንም የተጀመረ ምንም…
Read More
የእብድ ውሻ በሽታ በየዓመቱ ከ2700 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገድል ተገለጸ

የእብድ ውሻ በሽታ በየዓመቱ ከ2700 በላይ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገድል ተገለጸ

የግብርና ሚንስቴር እንደገለጸው በኢትዮጵያ የእብድ ውሻ በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሳ እና ስጋት እየሆነ በመምጣቱ  በዓመት እስከ 2 ሺህ 7 መቶ የሚደርሱ ሰዎች ይሞታሉ። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ጤናና ፐብሊክ ሄልዝ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር  ውብሸት ዘውዴ እንደተናገሩት ሁኔታው አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የኢትዮጵያ ክልል ከተሞች ትልቅ ስጋት ሆኗል፡፡ በከተሞች አካባቢ ባለቤት አልባ ውሾች በየመንገዱና በየጎዳናው የሚስተዋሉ በመሆናቸው  በርካታ ሰዎች በእብድ ውሻ በሽታ ተጠቂ እየሆኑ ነው ተብሏል። እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑ ህጻናት በበሽታው በስፋት እንደሚጠቁም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በሽታውን ለመከላከል እስከ 70 በመቶ የሚደርሱ ውሾች ቢከተቡ በሽታው ከውሻው ወደ ሰዎች እንዳይተላለፍ ማድረግ እንደሚቻልም ተገልጿል። አስቀድሞ በሽታው በሰዎች ህይወትና ደህንነት ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል  ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

ኢትዮጵያ ለታንዛኒያ ኤሌክትሪክ ሀይል እንደምትሽጥ ገለጸች

የኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለውጭ ሀገራት ከተሸጠ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 30 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን አስታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በተያዘው በጀት ዓመት ሁለት ሺህ ከ993 በላይ ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ይደረጋል፡፡ ለሦስት ጎረቤት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ማለትም ለሱዳን፤ ኬንያ እና ጅቡቲ 2 ሺህ 993 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ 182 ሚሊዮን ዶላር ወይም 10 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል፡፡ ለሀገር ውስጥ ደንበኞች በሚሸጥ የኤሌክትሪክ ሀይል ሽያጭ 20 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት መታቀዱንም አቶ ሞገስ ተናግረዋል፡፡ ባሳለፍነው የ2015 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት…
Read More
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ቻይና አመሩ

የቻይና ቤልት ኤንድ ሮድ ዓመታዊ ጉባኤ ከሁለት ቀናት በኋላ በቤጂንግ ይካሄዳል፡፡ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን መሪዎች በዚህ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቤጂንግ በማምራት ላይ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በዚሁ ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ ቻይና ማምራታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታውቋል፡፡ ቻይና ለኢትዮጵያ ብድር ከሚሰጡ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን በተለይም ለኤርፖርት ማስፋፊያ፣ ለመንገድ እና ለደረቅ ወደብ ልማት ግንባታዎች በቻይና ብድር ተገንብተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በጦርነት እና በኮሮና ቫይረስ መጎዳቱን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት የብድር ጫና ውስጥ በመግባቱ የብድር መክፈያ ጊዜ እንዲራዘምለት በመጠየቅ ላይ ነው፡፡ ቻይና የኢትዮጵያን የብድር መክፈያ ጊዜ በአንድ ዓመት ማራዘሟ የተገለጸ ሲሆን ከዓለም ባንክ…
Read More
በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ የዘር ማጥፋት ወንጀል ከፍተኛ ስጋት መኖሩን ተመድ አስታወቀ

በኢትዮጵያ በፌደራል መንግሥት የጸጥታ ሀይሎች እና በተለያዩ አካባቢዎች በሚገኙ ታጣቂዎች መካከል በቀጠለው ውጊያ ምክንያት፤ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች እንዲፈጸሙ የሚያስችል ከፍተኛ ስጋት መፍጠሩን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካሪ ገለጹ። የድርጅቱ የዘር ማጥፋት ወንጀል መከላከል ልዩ አማካሪ አሊስ ዋይሪሙ በኢትዮጵያ ስላለው ኹኔታ አስመልክተው ባወጡት መግለጫ፤ በትግራይ፣ አማራ፣ አፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች እየተካሄዱ ባሉ ውጊያዎች ምክንያት በአገሪቱ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት እና ተያያዠ አሰቃቂ ወንጀሎች የመፈጸም ኹኔታዎች እንዲኖሩ ማድረጉን ጠቁመዋል። "በኢትዮጵያ እየተፈጸሙ ስላሉት ወንጀሎች የተመለከቱ የሚደርሱን ሪፖርቶች እጅግ የሚረብሹ ናቸው" ያሉት ልዩ አማካሪዋ፤ "በአፋጣኝ ኹኔታውን ለመከላከል እርምጃ ሊወሰድ ይገባል።" ብለዋል። አክለውም፤ "እየደረሱን ካሉ ሪፖርቶች መካከል የአንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ግድያ እንደተፈጸመባቸው፣ ቤተሰቦች…
Read More
ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም ተጠየቀች

ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጎን እንድትቆም በኢትዮጵያ የእስራኤል ኤምባሲ ጥሪ አቀረበ የኢትዮጵያ መንግሥት እና ተቋማት፣ በሐማስ የተፈጸመውን ጥቃት እንዲያወግዙ፣ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለልኝ አድማሱ በሰጡት መግለጫ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት እስከ አሁን ስለጥቃቱም ይኹን ስለ ግጭቱ በይፋ የሰጠው መግለጫ የለም፡፡ ኾኖም፣ ኢትዮጵያ ገለልተኛ አቋም እንዳላትና ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንደምትፈልግ፣ በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር፣ ትላንት ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡ ሃማስ በእስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ  ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በሀገሪቱ የሚገኙ ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን ሰለባ መሆናቸዉን በኢትዮጵያ እስራኤል ኤምባሲ  አስታዉቋል፡፡ በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አለሊ አደማሱ እንዳሉት በወቅታዊ የጉዳቱን መጠን አሁን ላይ መግለጽ ባይቻልም ከተጎጂዎች መካከል ግን ቤተ እስራኤላዊያንና ኢትዮጵያዉያን እንደሚኖሩ ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ ከ1200 በላይ እስራኤላዉያን መሞታቸዉን አምባሳደር አለሊ…
Read More