Technews

ቴክኖ ሞባይል ካሞን 30 ፕሮ 5G የተሰኘ አዲስ ስልክ ይፋ አደረገ

ቴክኖ ሞባይል ካሞን 30 ፕሮ 5G የተሰኘ አዲስ ስልክ ይፋ አደረገ

ቴክኖ አዲሱን እና በቅርቡ በባርሴሎናው አመታዊ የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን ይፋ ያደረገውን ካሞን 30 ፕሮ 5G ሞዴል በይፋ በኢትዮጲያ አስተዋወቀ። የሞባይል ቴክኖሎጂን ጨምሮ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አምራች የሆነው እና ከ70 በላይ ሀገራት ምርቶቹን በስፋት የሚያቀርበው ቴክኖ አዲስ የሞባይል ቴክኖሎጂ ውጤት የሆነውን ካሞን 30 ፕሮ 5G ሞዴል በአዲስ አበባ ሸራተን አዲስ ሆቴል የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት አስተዋውቋል፡፡ አዲሱ ካሞን 30 ፕሮ 5G የሶኒ(SONY) የካሜራ ሴንሰር ቴክኖሎጂን ጨምሮ የተለያዩ የቴክኖ ምርምር ውጤት የሆኑ የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን አካቶ የተመረተ ሞዴል ነው። ቴክኖ በቅርቡ በስፔን ባርሴሎና በተካሄደው አንጋፍው እና አመታዊው የቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን (Mobile World Congress) ላይ ይህን አዲስ ካሞን 30 ፕሮ 5G ሞዴልን ጨምሮ የተለያዩ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ምርቶቹን በይፋ እንዳስተዋቀ የሚታወቅ…
Read More
የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የአሜሪካው ራክሲዮ የቴክኖሎጂ ኩባንያ የዳታ ማዕከሉን በኢትዮጵያ ከፈተ

የዳታ ማዕከሉ 30 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን በአፍሪካ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በአዲስ አበባ ከፍቷል። በአፍሪካ ገለልተኛ የመረጃ ማዕከል የሆነዉ ራክሲዮ ግሩፕ በኢትዮጵያ 2ኛዉን የዳታ ማዕከል በ30 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ወጪ ኢንቨስትመንት በመገንባት አስጀምሯል። ኩባንያው የዳታ ማዕከሉን በአዲስ አበባ በአይሲቲ ፓርክ ውስጥ መክፈቱን የገለጸ ሲሆን የዳታ ፍሰትን ሙሉ በሙሉ በአገር ዉስጥ በማድረግ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ድርጅቶች ለኢንተርኔት የሚያወጡትን ወጪ ለመቀነስ ይረዳል ተብላል። በኢትዮጵያ የተከፈተዉ አዲሱ የደረጃ III የመረጃ ማዕከል 800 ራኮች እና እስከ 3MW የአይቲ ሃይል አለዉ ተብሏል። በ2018 የተቋቋመዉ ራክሲዮ በአፍሪካ የመጀመሪያውን የዳታ ማዕከል በኡጋንዳ እንደከፈተ ገልጿል። ኩባንያው ሁለተኛውን የዳታ ማዕከል በኢትዮጵያ ዛሬ ያስጀመረ ሲሆን እስከ ሚቀጥለው ዓመት ድረስም በኮንጎ  ፣…
Read More