17
Nov
አቦል ቴሌቪዥን ከሰኞ ህዳር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሁለት አዳዲስ “ሀገርኛ” ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማዎችን ለተመልካቾቹ ላቀርብ ነው ብሏል፡፡ ለተመልካቾች የሚቀርቡት “ቁጭት” የተሰኘው ረጅምና ወጥ ሀገርኛ ተከታታይ ቴሌኖቬላ እና “ዳግማዊ” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው ድራማ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ይዘቶች አቦል ቴሌቪዥን ለደንበኞቹ ምርጥ ወጥ ሀገርኛ ይዘቶችን ለማቅረብ የወጠነውን ጅምር በተግባር የሚያረጋግጡና ቻናሉ የላቁ መዝናኛዎችን ለማቅረብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ናቸው። “ቁጭት” የተሰኘው ሀገርኛ ቴሌኖቬላ ታሪኩ የሚያጠነጥነው በሕይወት ጥቂት ወራት ብቻ እንደሚቀረው ከተነገረው በኋላ የናፈቀውን ልጁን ዮናስን ለማግኘት ፍለጋ በጀመረ አባት ነው፡፡ ድርጊቱ በተስፋ ማጣት እና በድህነት ውስጥ ያለን የሕይወት ውጣውረድም የሚያስቃኝ ሲሆን ዮናስ የአባቱን ህልውና እና ባለጸጋነት ታሪክ ሳያውቅ ሕይወቱ…