መነሻ ገፅ

የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ከሰሞኑ የስራ የመልቀቂያ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ማስገባታቸው ሲገለጽ ነበር። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በድረገጹ እንደገለጸው ከአሰልጣኝ ውበቱ ጋር በስምምነት መለያየቱን አስታውቋል። ፌዴሬሽኑ ከአሰልጣኙ የቀረበለትን የስራ መልቀቂያ ተቀብሎ ማጽደቁን ገልጾ አሰልጣኙ እስካሁን ላደረጉት ስራ ምስጋናውን አቅርቧል። አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በኢትዮጵያ ልምድ ካላቸው አንጋፋ አሰልጣኞች መካከል አንዱ ሲሆኑ ከኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ጋር በመሆን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አሸንፈዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ከ2020 ጀምሮ በማሰልጠን ላይ ያሉት አሰልጣኝ ውበቱ በኮትዲቯር አዘጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በጊኒ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ጨዋታዎችን ተሸንፈዋል። የ45 ዓመቱ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ የግብጽ ብሔራዊ ቡድንን 2 ለ 0 ማሸነፋቸውን ተከትሎ…
Read More
ተመድ በቶርች ጉዳይ ኢትዮጵያን ሊገመግም መሆኑን አስታወቀ

ተመድ በቶርች ጉዳይ ኢትዮጵያን ሊገመግም መሆኑን አስታወቀ

የተባበሩት መንግታት ድርጅት በፈረንጆቹ 1984 ላይ በእስረኞች የሚፈጸሙ ስቃዮችን ወይም ቶርቸርን ለመከላከል በማሰብ ስምምነት አዘጋጅቶ ነበር። ይህን ስምምነት ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የዓለማችን ሀገራት የተቀበሉት ሲሆን ትግበራው ግን ከቦታ ቦታ ይለያያል። የዚህ ስምምነት አዘጋጅ የሆነው ተመድ ስምምነቱን የተቀበሉ ሀገራት ህጉን እንዴት እየተገበሩት እንደሆነ ሊገመግም መሆኑን ለዓልዐይን በላከው መግለጫ አስታውቋል። ኢትዮጵያ ፣ ኮሎምቢያ፣ ብራዚል፣ ካዛኪስታን፣ ስሎቫኪያ እና ሉግዘምበርግ ደግሞ የሚገመገሙ ሀገራት ናቸው ተብሏል። 10 አባላት ያሉት የተመድ ገለልተኛ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ሀገራቱን በጀኔቫ እንደሚገመግሙም ተገልጿል። ይህ የባለሙያዎች ቡድንም የጸረ ቶርቸር ህግ ትግበራው ግምገማው የተገምጋሚ ሀገራት ተወካዮች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት ይገኛሉ ተብሏል። ግምገማውም ከሚያዚያ 9 ቀን እስከ…
Read More
መንግስት የጋዜጠኞችን እስር እንዲያቆም ተጠየቀ

መንግስት የጋዜጠኞችን እስር እንዲያቆም ተጠየቀ

የኢትዮጵያ ብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ማህበር በጋዜጠኞች እስር ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል። ማህበሩ እንዳለው ብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ስህተት በሚሰሩበት ወቅት ደግሞ በህግ አግባብ መጠየቅ እንዳለባቸው እና የህግ የበላይነት መከበር እንዳለበት እንደሚያምን ገልጿል። ይሁንን " ከለውጡ በኋላ " በሀገራችን የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት እንዲረጋገጥ ማህበራችን ብዙ ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ባለሙያዎች የሚሰሩበት አውድ እየጠበበ ጋዜጠኞች ስራቸውን በነፃነት እንዳይሰሩ በመንግስት የፀጥታ አካላት እየተሸማቀቁ እና እንግልት እየደረሰባቸው መሆኑን ማህበሩ በመግለጫው ላይ ጠቁሟል። የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማህበር መስራችና የስራ አስፈፃሚ አባል እንዲሁም የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ኃላፊ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውን ጨምሮ አራጋው ሲሳይ ፣ ገነት አስማማው ፣ ጌትነት አሻግሬ ፣ በየነ ወልዴና ቴዎድሮስ አስፋው…
Read More
በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ ከ2 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ውጪ መሆናቸው ተገለጸ

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ግጭት ለማስቆም በያዝነው ዓመት ሕዳር ወር የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል፡፡ ይሁንና የሰላም ስምምነት ቢፈረምም ከ2 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ የሕፃናት አድን ድርጅት/ሴቭ ዘ ችልድረን አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ እንዳለው የመማር ማስተማር ሂደቱን ለማስጀመር ተጨማሪ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ብሏል፡፡  በአሁኑ ወቅት በመላው ኢትዮጵያ ከ3 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሕፃናት በላይ ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ ሲሆን ይህም እድሜያቸው ለትምህርት ከደረሰ 16 ኢትዮጵያውያን ሕፃናት መሃከል አንዱ ከትምህርት ገበታ መገለሉን ያሳያል ተብሏል፡፡ ይህ አሃዝ ኢትዮጵያን ከትምህርት ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ቀውስ ካስተናገዱ ሃገራት አንዷ እንደሚያደርጋት ተገልጿል፡፡  በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ፣ በአማራ እና በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች በሚገኙ…
Read More
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው መታሰሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው መታሰሩ ተገለጸ

በበርካታ የኢትዮጵያ ብዙሃን መገናኛ ተቋማት በጋዜጠኝነት ሙያ ያገለገለው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በጽጥታ ሀይሎች መታሰሩን የስራ ባልደረቦቹ ለኢትዮ ነጋሪ ተናግረዋል ። ጋዜጠኛ ዳዊት ከሌሎች የስራ ባልደረቦቹ ጋር በመሆን አራት ኪሎ ሚዲያ የተሰኘ የድጅታል ሚዲያ አቋቁሞ በመስራት ላይ ይገኝ ነበር። ጋዜጠኛው ለስራ ወደ ባህርዳር ከተማ ባቀናበት ወቅት ዛሬ ሚያዝያ 4 ቀን 2015 ዓ.ም በጸጥታ ሀይሎች ተይዞ መወሰዱን ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የሙያ ባልደረቦቹ ነግረውናል። ይሁንና የአማራ ክልልም ይሁን የፌደራል መንግሥት በጋዜጠኛ ዳዊት እስር ጉዳይ እስካሁን ያሉት ነገር የለም። የሀገር መከላከያ ሰራዊት ህዝብ ግንኙነት ኮለኔል ጌትነት ስለ ጋዜጠኛው እስር እንደማያውቁ ተናግረዋል። ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት፣ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን፣ ኢትዮ…
Read More
መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ ኢሰመኮ አሳሰበ

መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ ኢሰመኮ አሳሰበ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሰሞኑ የክልል ልዩ ሀይሎችን በሚመለከት በተፈጠሩ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል። ተቋሙ እንዳለው የልዩ ሀይሎችን መልሶ የማደራጀትን ውሳኔ ትግበራ በውይይትና የሰዎችን ሰብአዊ መብቶች አደጋ ላይ በማይጥል ሁኔታ ሊከውን ይገባል ሲል አሳስቧል ኢሰመኮ መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎችን በፌዴራልና በክልል መደበኛ የጸጥታ ኃይሎች ውስጥ እንዲካተቱ በማድረግ መልሶ ለማደራጀት ያሳለፈውን ውሳኔና ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተነሱ ተቃውሞዎች፣ የጸጥታ መደፍረስ እና በአንዳንድ አካባቢዎች የደረሱ ግጭቶችንና ጉዳቶችን በተመለከተ ክትትል እያደረገ መሆኑን ገልጿል። ኮሚሽኑ በተለይም በቆቦ፣ በባሕር ዳር፣ በወረታ፣ በኮምቦልቻ፣ በደብረ ብርሃን እና በመራዊ የተቃውሞ ሰልፎች፣ መንገድ መዘጋት፣ የአገልግሎት መቋረጥ እንዲሁም በጸጥታ ኃይሎች መካከል ፍጥጫዎች የተከሰቱ ሲሆን፤ በአንዳንድ አካባቢዎች…
Read More
በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

በደብረ ብርሃን ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑ ተገለጸ

የደብረብርሃን ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሪት መሰረት መንገሻ እንደገለጹት ከትላንት ጀምሮ መርዝ ተጨምሮበት ውሃ ተበክሏል እየተባለ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተቋማቸው አንዱ ተግባሩ የሚያመርተውን ውሃ ጥራት አረጋግጦ ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት ሃላፊነታቸው በመሆኑን ባለሙያዎች እሁድ ቅዳሜን እና የበዓላትን ቀናት ጭምር አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡ የውሃ ማጠራቀሚያ ጋኖች ታጥረው የሚጠበቁ ከመሆኑም በላይ ሁል ጊዜ በባለሙያ ክትትል እየተደረገላቸው ውሃው በባለሙያ ጥራቱ ተረጋግጦ ለደንበኞች እንደሚሰራጭ አረጋግጠዋል፡፡ የፀጥታ ችግር ሲከሰት ደግሞ በልዩ ሁኔታ ጥበቃና ክትትል እንደሚደረግላቸው ጠቁመዋል፡፡ ችግር ካጋጠመም ውሃው እንደማይለቀቅ ጠቅሰው ህብረተሰቡ የውሃ ተቋሙ የሚያደርገውን ጥንቃቄ በአግባቡ ተረድቶ በአሉባልታ ወሬ እንዳይረበሽ መክረዋል፡ ውሃው 100 ፐርሰንት ንጹህ መሆኑን ስራ አስኪያጇ መልዕክታቸውን…
Read More
ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

ግብጽ የህዳሴው ግድብን ዓለም አቀፋዊ ከማድረግ እንድትታቀብ ኢትዮጵያ አሳሰበች

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ ዓለም በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል። ቃል አቀባዩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት ግብጽ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ተደጋጋሚ መግለጫዎችን እያወጣች ነው። መግለጫዎቹ ኢትዮጵያ በቀጣይ ክረምት ወራት ግድቡ ውሀ እንዲይዝ የተናጠል ውሳኔ እንዳትወስን የሚያሳስቡ ናቸው። በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄ "ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል ዙሪያ ማንንም የማስፈቀድ ግዴታ የለባትም" ብለዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ግዛት እና ሀብት እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ነው የሚሉት አምባሳደር መለስ በእቅዳችን እና በፕሮግራማችን እንመራለን ሲሉም አክለዋል። የግብጽ ሰሞንኛ ተደጋጋሚ መግለጫ የህዳሴው ግድብ አራተኛ ዙር ውሀ መመሙያ ጊዜ እየተቃረበ መምጣቱን ተከትሎ ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ለማድረግ ያለመ እንደሆነም ቃል አቀባዩ…
Read More
እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

እነ ዶክተር ሙሉቀን ሀብቱ ከተከሰሱበት የሙስና ወንጀል በነጻ ተሰናበቱ

ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነጻ ተባሉ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቴክኒክ ሙያና ስልጠና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሙሉቀን ሐብቱን ጨምሮ ከጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው አምስት ግለሰቦች በነጻ አሰናብቷቸዋል፡፡  ፍርድ ቤቱ ብይኑን የሰጠው ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 4፤ 2015 በዋለው ችሎት ነው፡፡  በዚሁ መዝገብ ክስ ከቀረበባቸው ግለሰቦች መካከል አንድ ተከሳሽ በሌሉበት ጥፋተኛ ሲባሉ፤ ቀሪ አምስት ተከሳሾች ደግሞ የተከሰሱበት ድንጋጌ ተቀይሮ እንዲከላከሉ በፍርድ ቤቱ በይኗል። ችሎቱ አምስት ተከሳሾችን በነጻ ያሰናበተው፤ “ዐቃቤ ህግ ባቀረበው የሰው…
Read More
ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

ግዙፉ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገለጸ

በቻይና በሲሚንቶ ዘርፍ የተሰማራው ግዙፉ ሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ መገንባት እንደሚፈልግ ገልጿል። በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው የሲኖማ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ሊቀመንበር እና የሲኤንቢኤም ተቋም ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ሚስተር ሉ ያን እና የሥራ ባልደረቦቻቸው ጋር ተወያይተዋል። ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስት በሚደረግበት ዙሪያ ቤጂንግ በሚገኘው የኩባንያው ዋና ጽ/ቤት ተገኝተው ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ተፈራ በውይይቱ ወቅት ኩባንያው በኢትዮጵያ ባሉት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች ከዲዛይን ጀምሮ በግንባታ ረገድ ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበው፣ በኢትዮጵያ ካለው የግንባታ ስፋት አንጻር የሲሚንቶ ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል። አምባሳደር ተፈራ አያይዘውም፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የሆነ የሲሚንቶ ፍላጎት ግምት ውስጥ በማስገባት በኢንቨስትመንቱ ዘርፍ ቢሰማራ የጋራ ተጠቃሚነቱ ሰፊ መሆኑን ገልጸዋል።…
Read More