መነሻ ገፅ

በኢትዮጲያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 7500 ደረሰ

በኢትዮጲያ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 7500 ደረሰ

በሳሙኤል አባተ በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ዓመታት በኮቪድ -19 ከ7 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር አስታውቋል። በኢትዮጲያ በሶስት ዓመት ውስጥ በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ሰው ሲጠቁ ከ7ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው እንዳለፈ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል ። ባለፉት ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በኮቪድ -19 በሽታ 500 ሺ 774 ሰዎች ሲያዙ ከነዚህም ውስጥ 7ሺህ 574 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ተገልጿል ። የኮቪድ-19 ክትባት በሶስት ዙር የተሰጠ መሆኑንና የተፈናቀሉ እና እስረኞች የክትባት ተከታታይ ተጠቃሚነት ላይ ቁጥሩ ዝቅተኛ እንደሆነ በጤና ሚኒስቴር የክትባት ኤክስፐርት የሆኑት ዶ/ር አለማየሁ አየለ ተናግረዋል ። በዓለም ላይ በኮቪድ -19 በሽታ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች እንደሚጠቁ…
Read More
ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኞችን ወደ ሳውዲ አረቢያ መላክ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን ወደ ሳውዲ አረቢያ ለመላክ በምልመላ ላይ እንደሆነች ተገልጿል። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴቶች የጅምላ ምልመላ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል ። የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች የሳውዲ አረቢያ የሰብዓዊ መብት አያያዟ ደካማ እንደሆነ ገልጸዋል። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለው የሴት ሠራተኞች የጅምላ ምልመላ አሳሳቢ ነው ብለዋል፡፡ አሁንም ቢሆን በርካታ ኢትዮጵያዊያን ሠራተኞች በሳውዲ አረቢያ ከሠራተኛ ሕጎች የተገለሉ እና በዘመናዊ ባርነት ስርዓት ለጥቃት የተጋለጡ ናቸው ተብሏል፡፡ “ካፋላ” በተሰኘው ስርዓት አንድ ሠራተኛ በደል ቢደርስባት እና ከአሠሪዎቿ ብትሸሽ ፓስፖርቷን ጨምሮ የተለያዩ የሰነድ መረጃዎቿን እንድታጣ እንደሚደረግ እና ይህ ስርዓት አሁንም ለውጥ እንዳልተደረገበት ተገልጿል። ‹‹ሳውዲ አረቢያ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በዘፈቀደ በማሰር እና አሰቃቂ…
Read More
ጉምቱው ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ኢዜማን ለቀቁ

ጉምቱው ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ኢዜማን ለቀቁ

አቶ አንዷለም ኢዜማን ተሻጋሪ ለማድረግ የሰነቅነው ህልም ምላሽ ሊያስገኝልኝ አልቻለም በሚል እንደለቀቁ በማህበራዊ ትስስእ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል። አቶ አንዷለም ኢዜማን ከመጠንሰስ እስከ መመሥረት፣ ከምሥረታ በኋላም በአባልነት ፓርቲውን በአመራርነት አገልግለዋል። አቶ አንዷለም ለፓርቲው ባስገቡት መግለጫ ላይ በፓርቲው ውስጥ የኢዜማ ስብራት ሲጠገን ለማየት አልቻልኩም ሲሉ ገልጸዋል። በፓርቲው ውስጥ በሚያነሱት ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ ማግኘት ባለመቻላቸው ማዘናቸውን ገልጸዋል። የፓርቲያችንን ቁመናና አሰላለፍ ከወዲሁ እናስተካክል የሚል ተማጽኖ ነበረኝ ያሉት አቶ አንዷለም ፓርቲው ይህንን እድል ሊፈጥር ባለመቻሉ መልቀቂያ ማስገባታቸውንም አክለዋል። ኢዜማ በ2014 በተካሄደው የኢትዮጵያ አጠቃላይ ምርጫ የግዢው ፓርቲ ሁነኛ ተፎካካሪ ነበር። ምርጫው…
Read More
በሱዳን የውጭ ሀገራት ኢምባሲዎች የጥቃት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ

በሱዳን የውጭ ሀገራት ኢምባሲዎች የጥቃት ሰለባ መሆናቸው ተገለጸ

በጀነራል አብዱልፋታህ አልቡርሃን የሚመራው የሱዳን ጦር እና በጀነራል ሀምዳን ዳጋሎ በሚመራው የፈጥኖ ደራሽ (RSF) መካከል ባለፈው ቅዳሜ የተቀሰቀሰው ጦርነት አራተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። በዚህ ጦርነት እስካሁን ከ200 በላይ ዜጎች ሲሞቱ ከ1500 በላይ ደግሞ መቁሰላቸውን የሱዳን ዶክተሮች ኮሚቴ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡ ከሟቾች ውስጥ ኢትዮጵያዊያንም ያሉበት ሲሆን የአንድ ቤተሰብ የሖነ አራት ዜጎችን ጨምሮ ዘጠኝ ኢትዮጵያዊያን መሞታቸው ተገለጿል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለም መቀመጫቸውን በሱዳን መዲና ካርቱም ያደረጉ የውጭ ሀገራት ኢምባሲዎች ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ፣አውሮፓ ህብረት፣ ኢትዮጵያ እና በርካታ የውጭ ሀገራት ኢምባሲዎች በካርቱም ከተማ እየተደረገ ባለው ጦርነት ሰለባ መሆናቸውን የየሀገራቱ ውጭ ጉዳጠይ ሚኒስቴሮች በትዊትር ገጻቸው ላይ ተናግረዋል፡፡ የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በካርቱም…
Read More
ለበዓል ልብስ አልተገዛልኝም በሚል ምክንያት ያኮረፈዉ ወጣት እራሱን አጠፋ

ለበዓል ልብስ አልተገዛልኝም በሚል ምክንያት ያኮረፈዉ ወጣት እራሱን አጠፋ

በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ለበዓል ልብስ አልተገዛልኝም በሚል ከቤተሰቦቹ ተጨቃጭቆ መግባባት ያልቻለዉ ወጣት በገመድ እራሱን ሰቅሎ ሕይወቱን ማጥፋቱ የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል። በደቡብ አሪ ወረዳ ባላመር ቀበሌ ነዋሪ የሆነዉ ወጣቱ ለ2015 የትንሳኤ በዓል ልብስ እንዲገዛለት ለወላጆቹ ጥያቄ ያቀርባል። ወላጆቹ ቀደም ሲል የሚለብሳቸዉን ልቦሶች አጽድቶ በመልበስ የዘንድሮዉን በዓል አክብሮ እንዲዉልና በሱ ጥያቂነት ሳይሆን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ቤተሰብ ይገዛልሀል የሚል ተስፋ አስቆራጭ ምላሽ ይሰጠዋል። በወላጆቹ እምቢታ የተበሳጨው ይህ ወጣቱ እራሱን እንደሚያጠፋ ዝቶ ከቤተሰቦቹ ጋር ከስምምነት ሳይደርስ መለያየቱን ፖሊስ ገልጿል። ወጣቱ እራሱን ለማጥፋት ቢዝትም ቤተሰብ እንዲህ አይነቱን ተግባር አይፈጽምም የሚል እምነት እንደነበራቸው ተናግረዋል ። ይሁንና ወጣቱ ሚያዝያ 08 ቀን 2015…
Read More
በሱዳን የሚገኙ አምስት ኢትዮጵያውያን መገደላቸው ተገለጸ

በሱዳን የሚገኙ አምስት ኢትዮጵያውያን መገደላቸው ተገለጸ

በሱዳን መከላከያና በፈጥኖ ደራሽ ሐይል መካከል በካርቱምእና አካባቢው የተነሳው ጦርነት በከተማዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን ችግር ላይ እንደጣላቸው ተገልጿል። በስፍራው የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እንደነገሩን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ችግር ላይ ናቸው። ኢትዮጵያዊያን በግለሰቦች ቤት ተጠልለው እንደሚገኙም የተገለጸ ሲሆን በተኩስ ልውውጡ የሞቱ እና የቆሰሉ መኖራቸውንም ሰምተናል። በጀነራል አቡድልፋታህ አልቡርሃን የሚመራው የሰዱን ጦር እና በጀነራል ሀምዳን ዳጋሎ ወይም ሄመቲ ሀይሎች መካከል ይፋዊ ጦርነት ሲካሄድ ዛሬ ሶስተኛ ቀኑ ላይ ይገኛል። እስካሁን በዘለቀው ጦርነት ከ100 በላይ ንጹሀን ሲገደሉ ከ600 በላይ ዜጎች ደግሞ ቆስለዋል ተብሏል። አሜሪካ፣ አውሮፓ ህብረት፣ ሩሲያ፣ ሳውዲ አረቢያ እና በርካታ የዓለማችን ሀገራት ተፋላሚ ወገኖች ጦርነት እንዲያቆሙ በማሳሰብ ላይ ናቸው። በካርቱም ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ዜጎች ከቤት እንዳይወጡ እና…
Read More
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የቡና ሳይንስ ምሁራን ሊኖሯት ነው

ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የቡና ሳይንስ ምሁራን ሊኖሯት ነው

ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ ትምህርት መስክ የተማሩ ተማሪዎች ሊመረቁ ነው። የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2015 የትምህርት ዘመን መጨረሻ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 37 ተማሪዎችን በ " ቡና ሳይንስ " የትምህርት መስክ ያስተማራቸውን ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ አሳውቋል። ዩኒቨርሲቲው የቡና ምርት ኢትዮጵያ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ሸቀጥ በመሆኑ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ 37 ተማሪዎችን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ የትምህርት መስክ ይመረቃሉ ብሏል። ኢትዮጵያ ቡናን ለዓለም ያበረከተች ሀገር ብትሆንም እስካሁን ድረስ የቡና ትምህርት መስክ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት አዳጋች ሆኖ ነበር ያለው ተቋሙ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቡና ሳይንስ ትምህርት ክፍል እራሱን ችሎ በ2012 ዓ.ም እንዲከፈት ማድረጉን አስታውሷል ። በቡና ምርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመመርመር ከዘርፉ ተጠቃሚ…
Read More
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የገንዘብ ድጋፍ ማረጋገጫ አገኘች

ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ እን አይኤምኤፍ ጋር ስታደርገው የነበረው ውይይት ተጠናቋል። የኢትዮጵያ የፋይናንስ ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘባ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ሃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ለአንድ ሳምንት ሲያደርግ የነበረውን ውይይት አጠናቅቋል፡፡ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሽ በቀለ በትዊተር ገጻቸው እንዳስታወቁት በገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ እና በብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተመራው ልዑክ ከዓለም ባንክ እና ከዓለማቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ዳይሬክተሮች ጋር ሲያደርግ የነበረው ውይይት ተጠናቋል፡፡ የፋይናንስ ልዑኩ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አይ ኤም ኤፍ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እና ልዑካቸው ጋር ምክክር ማድረጋቸውን እና ለአንድ ሳምንት የቆየውን ውይይት መጠናቀቁን አንስተዋል፡፡ የተደረገው ውይይት ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የልማትና ሰብዓዊ  ድጋፍ ለማግኘት…
Read More
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ የበለጠ አጓጊ ሆኗል

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ የበለጠ አጓጊ ሆኗል

የፕሪሚየር ሊጉ መሪ አርሰናል ነጥብ ጣለ። በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ 31ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አርሰናል ከ ዌስትሀም ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል። የአርሰናልን ግቦች ጋብሬል ጄሱስ እና ማርቲን ኦዴጋርድ ሲያስቆጥሩ የዌስትሀምን የአቻነት ግቦች ቤንራህማ እና ጃርድ ቦውን አግብተዋል። የአርሰናል የመሀል ሜዳ ተጨዋች ማርቲን ኦዴጋርድ በውድድር አመቱ አስራ አንደኛ ግቡን ከመረብ ማሳረፍ ችሏል። ከሜዳው ውጪ የተጫወተው አርሰናል በሊጉ ደረጃ ሰንጠረዥ ነጥቡን ሰባ አራት ያደረሰ ሲሆን ቀሪ ጨዋታ ካለው ተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለው የነጥብ ልዩነት ወደ አራት ዝቅ ብሏል። ዌስትሀም በበኩሉ በ31 ነጥብ አስራ አምስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል። በቀጣይ የእንግሊዝ መርሀ ግብር አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን እንዲሁም ዌስትሀም ከ በርንማውዝ…
Read More
ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ፍርድ ቤት ቀረቡ

ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው እና ቴዎድሮስ አስፋው ፍርድ ቤት ቀረቡ

ሕገመንግስቱንና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ ተንቀሳቅሰዋል በማለት ተጠርጥረው ከአራት ቀናት በፊት ታስረው የነበሩት ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻውና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው ዛሬ ሚያዚያ 7 ቀን 2017 ዓም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው የምርመራ ጊዜ ተጠየቀባቸው። ፖሊስ ተጠርጣሪ ጋዜጠኞቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ ጊዜ ቀጠሮ የጠየቀባቸው፣ ጋዜጠኛ ዳዊት አራት ኪሎ ሚዲያ፣ የሚባል የኦንላይን ሚዲያ ፈቃድ ሳይኖረው በመክፈት ሕገመንግስቱንና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ ሕዝብን ከሕዝብ ጋር ለማጋጨትና አንዱን ሐይማኖት ከሌላው ጋር ለማጋጨት በሕገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ እንደደረሰበት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። በተመሳሳይ ሁኔታ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስም ኢትዮ ሰላም የሚባል የኦንላይን ሚዲያ ፈቃድ ሳይኖረው በመክፈት ሲሰራ እንደነበርና ሁለቱንም ተጠርጣሪዎች እየመረመረ መሆኑን አስረድቶ ለተጨማሪ…
Read More