08
Apr
በአማራ ክልል ለሶስተኛ ቀን ተቃውሞ ቀጥሏል የፌደራል መንግሥት የተማከለ የጸጥታ ሀይል ለመመስረት ማቀዱን ተከትሎ የክልል ልዩ ሀይሎች እንዲፈርሱ ውሳኔ አስተላልፏል። ህጋዊ መሰረት የለውም የሚባለው የክልል ልዩ ሀይል አባላት ወደ ፌደራል ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ እና መደበኛ ፖሊስ እንዲደራጁም ትግበራ መጀመሩን የፌደራል መንግሥት አስታውቋል። ይሁንና በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የመንግሥትን ውሳኔ የተጠራጠሩ እና የተቃወሙ ሰዎች ወደ አደባባይ ለተቃውሞ ወጥተዋል። በተለይም በሰሜን ወሎ፣ ጎጃም እና ሌሎችም አካባቢዎች መንገዶች በተቃዋሚዎች የተዘጉ ሲሆን ወደ ዋና ከተማ አዲስ አበባ የሚያስገቡ መንገዶችም ተዘግተዋል። ይህን ተከትሎም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የሚያስኬዱ መንገዶች በከፊል ተዘግተዋል። ህዝቡ ወደ አደባባይ የወጣው የትግራይ…