ዜና

ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ሱዳን የኢትዮጵያ 70 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ እዳ እንዳለባት ተገለጸ

ጎረቤት ሀገር ሱዳን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ከሚገዙ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን ለዓመታት የተጠቀመችበትን እዳ አልከፈለችም ተብሏል፡፡ ሱዳን ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ የተጠቀመችበትን 70 ሚሊዮን ዶላር እዳዋን ባለመክፈሏ ምክንያትም የሚቀርብላት የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን በ50 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡ ካሳለፍነው ሚያዚያ ወር ጀምሮ በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሱዳን ከ8 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የተፈናቀሉ ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ግብጽ  እና ቻድ ደግሞ ሱዳናዊያን የተጠለሉባቸው ሀገራት ናቸው፡፡ ኢትዮጵያ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ለጎረቤት ሀገራት ከሸጠችው የኤሌክትሪክ ሽያጭ 66 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 47 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የፌደራል ኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል። ሱዳን ባለባት የጸጥታ ችግር ምክንያት ከዚህ በፊት የተጠቀመችበትን የኤሌክትሪክ ኃይል ክፍያ በወቅቱ መክፈል አለመቻሏ ለገቢው…
Read More
ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላ ድጋፉን አድርገዋል ተብሏል። ሚንስትሩ ከጉብኝታቸው በኋላ እንዳሉት አሳሳቢ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀጣይ ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ይደርሳክ ብለዋል። የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፉ ለሶስት ሚሊየን ሰዎች ህይወት አድን እርዳታ ለማቅረብ እንደሚውልም ተገልጿል። አስቸኳይ ድጋፉ በአልሚ ምግብና ሌሎች ወሳኝ ግብአቶች ምክንያት እየተከሰተ የሚገኘውን ሞት ለመቀነስ ለ75 የጤና ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን ለማቅረብ ነውም ተብሏል። የአውሮፓ ህብረት ከአንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ በድርቅ እና ግጭቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በጦርነት እና ድርቅ ምክንያቶች ለእርዳታ የሚዳረጉ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመምጣት ላይ ይገኛል።…
Read More
ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ 10 ቢሊዮን ዶላር ብድር መክፈሏ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት በመሻሻል ላይ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ (ዶ/ር) የመንግስታቸውን የስድስት ወራት አፈጻጸም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሌት “ህገ መንግስት ጋር ተያይዞ ከአማራ ክልል ለሚነሳው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሟል፤ ስራውን እየሰራ ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የአማራ ህዝብ በስራ ላይ ባለው ሕገ መንግስት ምክንያት ተንቀሳቅሶ መስራት፣ ሀብት ማፍራት ሌሎች የማንነት ጥያቄዎች እንዳይፈቱ አድርጓል የሚል ጥያቄ አላቸው፡፡ በዚህም መሰረት የአማራ ህዝብ ይህ በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት ሲዘጋጅ እና ሲጸድቅ በቂ ውይይት እንዳልተደረገበት እንዲሁም የአማራ ህዝብን አግላይ ነው በሚል ጥያቄዎችን ሲያነሱ ቆይተዋል፡፡ ለአብነትም የአማራ ክልል ወሰን አከላለል ትክክል…
Read More
ቱርክ በጦር መሳሪያ የተጎዳው አል ነጃሺ መስጅድን ለማደስ ጥያቄ አቀረበች 

ቱርክ በጦር መሳሪያ የተጎዳው አል ነጃሺ መስጅድን ለማደስ ጥያቄ አቀረበች 

 ታሪካዊው የኢትዮጵያ ቅርስ አል ነጃሺ መስጅድ በትግራይ ክልል የሚገኝ ሲሆን በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ወቅት በከባድ መሳሪያ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ቱርክ ይህንን ታሪካዊ የእስልመና ቅርስ ለማደስ ለኢትዮጶያ መንግስት ጥያቄ እንዳቀረበች የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን  አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴሩ እና የትግራይ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ቅርሱ በሚታደስበት ሁኔታ ከቱርክ የቀረበውን ጥያቄ መቀበላቸው ተገልጿል፡፡ ቅርሱ በሚታደስበት ሁኔታም የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጀምረዋል የተባለ ሲሆን የቱርክ ቅርስ ጥገና ባለሙያዎች ወደ ቦታው አምርተው ምልከታ መጀመራቸውን የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ አበባው አያሌው ተናግረዋል፡፡  ለቅርሱ እድሳት የሚያስፈልገው በጀት ምን ያህል እንደሆነ እና ምን ያህል ገንዘብ እንደሚፈጅ ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡ ለሁለት ዓመት በተካሄደው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት አል ነጃሺ መስጂድ…
Read More
ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከቆዳ እና ማዕድናት ንግድ 200 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

በ2016 በጀት ዓመት ሥድስት ወራት 100 ሚሊየን ዶላር ማጣቱን የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር አስታውቋል። የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፀሐፊ እንዳለ ሰይፉ፥ ባለፉት ሥድስት ወራት 124 ሚሊየን ዶላር ከቆዳ ምርቶች ሽያጭ ለማግኘት ታቅዶ መሰራቱን ተናግረዋል። ይሁን እንጅ ማሳካት የተቻለው 14 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር ብቻ መሆኑን ተናግረው በግማሽ ዓመቱ የተገኘው ገቢ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ3 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር ቅናሽ አሳይቷል። የቆዳ ዘርፉ ከ2010 ዓ.ም በኋላ ባሉት ተከታታይ ዓመታት ከፍተኛ የገቢ ማሽቆልቆል እንዳጋጠመውም አስረድተዋል። የውጭ ምንዛሬ እጥረት፣ የሥራ ማስኬጃ በጀት እጦትና ለዘርፉ የተሰጠው የትኩረት ማነስ ለገቢው መቀነስ ዋነኛ ምክንያቶች መሆናቸውንም ገልጸዋል። በውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያትም የቆዳ ፋብሪካዎች ከሥራ…
Read More
ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

ኢትዮጵያ ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘርባትን ጥቃት ለመመከት ጦሯ ዝግጁ መሆኑን ገለጸች

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፎልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እንዳሉት ሰራዊቱ “ከየትኛውም አቅጣጫ የሚሰነዘርበትን ጥቃት” ለመመከት ዝግጁ ነው ብለዋል፡፡ ዋና አዛዡ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ በሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሰልጠኛ ለ24ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መኮንኖች ባስመረቀበት ወቅት እንዳሉት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ወቅት “በሰላማዊ መንገድ የባህር በር ለማግኘት ጥረት እያደረገች ያለችበት ነው” ያሉት አዛዡ የሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች የውስጥ ችግሮችን ለማባባስ “የቋመጡበት እና የቆረጡበት” ወቅት እንደሆነም ተናግረዋል። ኢትዮጵያ “ከቀይ ባህር ተገፍታ በመቆየቷ የደረሰባትን የኢኮኖሚና የጸጥታ ተግዳሮቶችን እና ስብራቶችን” ለመቅረፍ “እየሞከረች” ያለችበት መሆኑን ልብ ሊሉት እንደሚገባ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ለተመራቂ ወታደራዊ መኮንኖቹ አሳስበዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ…
Read More
በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ከ50 በላይ ንጹሃን ዜጎች በመከላከያ ሰራዊት ተገደሉ

ከአማራ ክልል ዋና ከተማ ከሆነችው ባህርዳር በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው መራዊ ከተማ ከሰሞኑ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች እና ፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከባድ ውጊያ ተቀስቅሶ ነበር፡፡ በዚህ ውጊያ ምክንያት የፋኖ ታጣቂዎች የመራዊ ከተማን ተቆጣጥረው የነበረ ቢሆንም በኋላ ለቀው መሄዳቸውን ተከትሎ ወደ ከተማው የገባው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ50 በላይ የከተማዋ ነዋሪዎችን እንደገደሉ ቢቢሲ ነዋሪዎችን አነጋግሮ ዘግቧል፡፡ እንደ ነዋሪዎቹ አስተያየት ከሆነ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ነዋሪዎቹን ከመንገድ ላይ እና መኖሪያ ቤታቸው በማሰባሰብ ገድለዋቸዋል፡፡ በአማራ ክልል በርካታ አካባቢዎች ከባድ ውጊያ እየተካሄደ ሲሆን የፋኖ ታጣቂዎች በተለይም የገጠር አካባቢዎችን ተቆጣጥረው ሲያዙ ከተሞች ደግሞ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ተይዘዋል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት…
Read More
ኢትዮጵያ ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራን ከሁለት ዓመት በኋላ እንደምታካሂድ ገለጸች

ኢትዮጵያ ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራን ከሁለት ዓመት በኋላ እንደምታካሂድ ገለጸች

በኢትዮጵያ የህዝብ እና ቤት ቆጠራ ከተደረገ 17 ዓመት የሆነው ሲሆን የሕዝብ ቁጥሯን በየዓመቱ 10 በመቶ እየጨመረች እየቆጠረች ትገኛለች፡፡ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ የጦርነት እና ጸጥታ ችግሮች የሕዝብ ቆጠራውን ለማካሄድ እንቅፋት ሆኖ የቆየ ሲሆን በየጊዜው የፕሮግራም ማራዘም ስታደርግም ነበር፡፡ ከሶት ዓመት በፊት ብሔራዊ የሕዝብ ቆጠራ ለማድረግ አራት ቢሊዮን ዶላር በጀት ተመድቦ የባለሙያ እና ቁሳቁስ ዝግጅት የተጀመረ ቢሆንም በሀገሪቱ ባጋጠመ ጦርነት ምክንያት ሳይካሄድ ቆይቷል፡፡ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ 4ኛዉ የህዝብ እና ቤት ቆጠራን እስከ 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ለማከናወን ማቀዱን አስታውቋል። ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው ለሶስት ዓመታት በፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ስታትስክስ አገልግሎት የተዘጋጀውን የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ ልማት ፕሮግራም ይፋ ባደረገበት…
Read More
በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ

በአማራ ክልል የተጣለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለአራት ወራት ተራዘመ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ባሳለፍነው ነሀሴ ለስድስት ወራት የታወጀው አስቸኳይ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት ተራዝሟል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ልዩ ስብሰባ በአማራ ክልል የታወጀውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተጨማሪ አራት ወራት  አራዝሟል። የምክር ቤቱ አባላት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዙሪያ አደረጉት በተባለው ውይይት ከዋጁ በሁለት ተቃውሞ በሶሰት ድምፅ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ ለአራት ወራት እንዲራዘም መወሰኑ ተገልጿል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ…
Read More
ኢትዮጵያ ከተመድ የ28 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ አገኘች

ኢትዮጵያ ከተመድ የ28 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ አገኘች

የተገኘው በጀት የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪን ምርታማነት ለማሳደግ እና ለማዘመን እንደሚውል ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግስታት የኢንዱስትሪ ልማት ድርጅት (ዩኒዶ) የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪን ለማልማት የሚያስችል የ28 ሚሊየን ዶላር ሥምምነት ተፈራርመዋል። ሥምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና የዩኒዶ የኢትዮጵያ ተወካይ ካልባሮ አውሬሊያ ፓትሪዚያ ተፈራርመውታል። ፕሮጀክቱ በመጪዎቹ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ልማት ኢንስቲትዩት በኩል የሚተገበር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል። በተጨማሪም የዘርፉን ኢኮኖሚ ለማስተዋወቅና የቴክኖሎጂ ልማትን ለማሳደግ እንዲሁም የሚለቀቁ ተረፈ ምርቶችን በመቀነስ መልሶ ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመተግበር እንደሚያስችልም በስምምነቱ ወቅት ተገልጿል። ኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሀገራት መካከል አንዷ የነበረች ቢሆንም ባለፉት ዓመታት ውስጥ በጦርነት ውስጥ መቆየቷ…
Read More