Britain

ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

ብሪታንያ በኢትዮጵያ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

የብሪታንያ የአፍሪካ ልማት ዳይሬክተር በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ከጉብኝቱ በኋላ ድጋፉን አድርገዋል ተብሏል። ሚንስትሩ ከጉብኝታቸው በኋላ እንዳሉት አሳሳቢ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር በቀጣይ ወራት 10 ነጥብ 8 ሚሊየን ይደርሳክ ብለዋል። የ125 ሚሊየን ዶላር ድጋፉ ለሶስት ሚሊየን ሰዎች ህይወት አድን እርዳታ ለማቅረብ እንደሚውልም ተገልጿል። አስቸኳይ ድጋፉ በአልሚ ምግብና ሌሎች ወሳኝ ግብአቶች ምክንያት እየተከሰተ የሚገኘውን ሞት ለመቀነስ ለ75 የጤና ተቋማት የተለያዩ ድጋፎችን ለማቅረብ ነውም ተብሏል። የአውሮፓ ህብረት ከአንድ ወር በፊት በኢትዮጵያ በድርቅ እና ግጭቶች ለተፈናቀሉ ዜጎች 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ በጦርነት እና ድርቅ ምክንያቶች ለእርዳታ የሚዳረጉ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ የመጣ በመምጣት ላይ ይገኛል።…
Read More
ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ብሪታንያ ከመቅደላ የዘረፈቻቸውን ቅርሶች ለኢትዮጵያ አስረከበች

ከመቅደላ ተዘርፈው የተወሰዱ የተለያዩ የኢትዮጵያ ቅርሶች በለንደን ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተመለሱ በ1868 በአጼ ቴዎድሮስ ዘመነ መንግሥት በብሪታንያ ተዘርፈው የተወሰዱ የኢትዮጵያ ቅርሶች መመለሳቸውን በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡ ከተመለሱት ቅርሶች መካከል በ1868 ዓ.ም ከመቅደላ የተዘረፈ የመድሃኒያለም ታቦት፣ የልኡል አለማየሁ የጸጉር ዘለላ፣ ከብር የተሰሩና በነሃስ የተለበጡ ሦስት ዋንጫዎች እንዲሁም በዘመኑ ጦርነት ላይ የዋለ የጦር ጋሻ እንደሚገኙበት ገልጿል፡፡ ለንደን በሚገኘው የአቴናየም ክለብ በተካሄደው የቅርሶቹ ርክክብ ሥነ ስርዓት ላይ፤ በዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ልኡካን ቡድን፣ የብሄራዊ ቅርስ አስመላሽ ኮሚቴ ተወካይ፣ የብሪታኒያ ፓርላማ አባላት፣ ቅርሶቹን ለማሰመለስ የተባበሩ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በመርሀ ግብሩ ላይም አምባሳደር ተፈሪ መለሰ፤ የተመለሱት የተለያዩ…
Read More