ዜና

የምርጫ ቦርድ አዲስ አሰራር ተፅዕኖ እንደሚፈጥርባቸዉ ፓርቲዎች አስታወቁ

የምርጫ ቦርድ አዲስ አሰራር ተፅዕኖ እንደሚፈጥርባቸዉ ፓርቲዎች አስታወቁ

ስምንት የፖለቲካ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ የዘረጋው አዲስ አሰራር በቀጣዩ ሀገር አቀፍ ምርጫ ላይ ተጽዕኖ እንደሚፈጥርባቸው አስታውቀዋል። የቦርዱን አዲስ አሰራር የተቃወሙ ፓርቲዎች የህብር ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ  ፓርቲ (ህብር ኢትዮጵያ)፣ መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)፣ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ( ባልደራስ) ትብብር ለኢትዮጵያ  አንድነት ፓርቲ፣ለኢትዮጵያ አማራ ግዮናዊ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ)፣የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)፣የዎላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ (ዎብን) ፓርቲዎች ናቸው። በዚህ በጋራ መግለጫቸው የሀገሪቱ አቅም ባልፈቀደበትና እንደ ሀገር  ግንዛቤ በሌለበት ቴክኖሎጂካል አሰራር  ለመስፈርትነት መጠቀም አግባብነት የለውም ብለዋል። አካል ጉዳተኞች ከሁለት ሆስፒታሎች ማስረጃ እንዲያቀርቡ ግዴታ መቀመጡ፣ የአገሪቱን ገጠር አካባቢዎች ያላገናዘበና ሆስፒታሎች በሌሉበት ማስረጃ  መጠየቅ የአካል ጉዳተኞች ነባራዊ ሁኔታ የሚዳሰስና የሚታይ ሆኖ ሳለ ማስረጃ መጠየቁ በራሱ…
Read More
ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ ተስማማች

ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ብራዚል እና ደቡብ አፍሪካ ጋር የእስረኞች ልውውጥ ለማድረግ ተስማማች

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ስብሰባው በቻይና እስር ቤት ለረጅም ጊዜ በሞት ፍርድ ጥላ ስር የምትገኘውን ኢትዮጵያዊቷን ናዝራዊት አበራን ወደ ሀገሯ ለመመለስ መፍትሔ ይሰጣል የተባለለትን የፍርደኞች ማስተላለፍ ስምምነት አዋጅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ይህንን ስምምነት ያጸደቀው ከቻይና በተጨማሪ ከብራዚል ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ጋር የተደረገውን የፍርደኞች ማስተላለፍ እና ከደቡብ አፍሪካ ጋር የተፈረመውን በወንጀል የሚፈለጉ ሰዎችን አሳልፎ የመስጠት ስምምነቶችን ጨምሮ ነው። በውይይቱ ወቅት በተለይም ከቻይና ጋር የተደረገው ስምምነት ለዓመታት በፍርድ ሂደት ላይ የምትገኘውን ናዝራዊት አበራን ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት ትልቅ የሕግ ማዕቀፍ እንደሚሆን ተገልጿል። ይሁን እንጂ በዕለቱ የምክር ቤት አባላት በስምምነቱ ላይ የተለያዩ አመለካከቶችን ያነሱ ሲሆን የሁለቱ ወገኖች የክርክር ነጥብም የአዋጁን አስፈላጊነትና የሉዓላዊነት…
Read More
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ3ኛ ጊዜ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ወጪ አሜሪካ መሸፈኗን ተናገሩ

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለ3ኛ ጊዜ የህዳሴውን ግድብ ግንባታ ወጪ አሜሪካ መሸፈኗን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ስልጣን የመጡበትን አንደኛ ዓመት አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ወጪ በሀገራቸው መሸፈኑን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ላይ በቆዩባቸው ጊዜያት ስምንት ጦርነቶችን እንዳስቆሙ ገልጸው ኢትዮጵያ እና ግብጽም በህዳሴው ግድብ ምክንያት ሊያደርጉት የነበረውን ጦርነት ማስቆማቸውን ገልጸዋል። "ኢትዮጵያ በናይል ወንዝ ላይ በገነባችው ትልቅ ግድብ ምክንያት ግብጾች ተጎድተዋል፣ ውሀቸው ቀንሶባቸዋል፣ ናይል ግብጽ ውስጥ ያለ ነበር እሚመስለኝ፣ ወንዙ ይህን ጉዳይ መፍታት እፈልጋለሁ" ብለዋል ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ። "የግድቡን ግንባታ ወጪ ማን እንደሸፈነው ታውቃላችሁ? እኛው ነን" ያሉት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢትዮጵያ እና ግብጽ መካከል ያለውን አለመግባባት የመፍታት እቅድ እንዳላቸውም ተናግረዋል። ስለ ኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የሚሰሙት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዚህ በፊትም…
Read More
በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በህገወጥ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ወደ ዱባይ ሲልክ የነበረው ሰው በ20 ዓመት እስራት ተቀጣ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ  ቢቂላ ከተማ ውስጥ ነዋሪ የሆነው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣያገኝ ሰዎችን ወደ ዱባይ የሚልከው ግለሠብ በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ አስታዉቋል። የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ ዋና መምርያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሐላፊ ዋና ኢንስፔክተር ከድር ጅቦ እንደተናገሩት ተከሣሽ ገመቹ  ሰይድ የተባለው ግለሠብ ከሚመለከተው አካል እውቅና ፈቃድ ሣይኖረው  በዶዶላ ወረዳ ቢቂላ ከተማ ነዋሪ የሆኑ ሁለት ግለሠቦችን ከፍተኛ የስራ ልምድና ችሎታ  ስላላችሁ ስራ የማግኘት እድላችሁ ሰፊ ነው በማለት የማታለያ ቃል በመጠቀም ወደ ዱባይ እንደላካቸው ገልፀዋል። ተከሣሹ የተለያዩ  አሣማኝና  ማታለያ ቃላቶችን በመጠቀም ከሁለቱ ግለሠቦች 250 ብር በአጠቃላይ 500 ሺህ ብር በመቀበል ወደ ተባበሩት አረብ ኢምሬት ዱባይ ከተማ የላካቸው መሆኑ…
Read More
ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኢትዮጵያ ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርትን ለዓለም ገበያ አስተዋወቀች

ኦሪጅናል ቴፍ-ሊ የተባለው ከጤፍ የተሰራ የወተት ምርት ዛሬ በለንደን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና በአምራቾቹ ትብብር በተዘጋጀ የማስተዋወቂያ መድረክ ላይ ይፋ ተደርጓል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ከንግድ ማህበረሰቡ፣ ከሚዲያ፣ ከእንስሳት ተዋጽኦዎች ነፃ በሆኑ ምግቦች ምርት እና ግብይት ውስጥ የሚሳተፉ ኢንዱስትሪዎች አባላት እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተገኝተዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ከእፅዋት የተዘጋጁ የምግብ አማራጮች ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱ የሚታወቅ ሲሆን ዝግጅቱ ጤፍን ለአለም አቀፍ ታዳሚዎች የበለጠ ለማስተዋወቅ እድል ፈጥሯል። በብሪታንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ብሩክ መኮንን በመክፈቻ ንግግራቸው ጤፍ በኢትዮጵያዊያን የአመጋገብ ዘይቤ ውስጥ ያለውን ሰፊ ቦታ እንዲሁም የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም በሚችሉ የምግብ ስርዓቶች ጥናቶች ላይ ሊያበረክት ስለሚችለው አዎንታዊ አስተዋጽኦ አብራርተዋል፡፡ የኦሪጅናል ቴፍ-ሊ (The Original Teff-ly) መስራቾች…
Read More
አይሾው ስፒድ የተሰኘው ተጽዕኖ ፈጣሪ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ከ240 ሺህ በላይ ሰብስክራይበር ማግኘቱ ተገለጸ

አይሾው ስፒድ የተሰኘው ተጽዕኖ ፈጣሪ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ከ240 ሺህ በላይ ሰብስክራይበር ማግኘቱ ተገለጸ

አሜሪካዊው ተጽዕኖ ፈጣሪ ዩቲዩበሩ I show speed በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ የአንድ ቀን ቆይታ አድርጓል። ግለሰቡ በኢትዮጵያ በነበረው ቆይታ ሳይንስ ሙዚየም፣ አድዋ ሙዚየም፣ ስላሴ ካቴደራል ቤተ ክርስቲያን ፣ በመስቀል አደባባይ እና ሌሎችም ቦታዎችን በመጎብኘት የዓለም ትኩረት ስቧል። ዩቲዩበሩ በአዲስአበባ ጥሩ የሚባል አቀባበል ተደርጎለት እሱም እያመሰገነ ይገኛል። በኢትዮጵያ ቆይታዉ ብቻ ከ 250 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን ማግኘቱንም በመገረም ሲናገር ታይቷል። ስፒድ በአዲስ አበባ ቆይታዉ በጥሩ መልኩ የኢትዮጵያን መልክ ለማሳየት የተደረጉ ጥረቶች መልካም የሚባሉ ነበሩ። የኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴርም አጋጣሚዉን በጥሩ የተጠቀመበት ሲሆን የወርቅ ብራስሌት፣ ጥሬ ስጋ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቪዬሽን ማሰልጠኛ እና ሌሎች ታሪካዊ ሁነቶችን ተከታትሏል። የቱሪዝም ሚንስትር ሰላማዊት እና በሚስወርልድ ውድድር…
Read More
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገደሉ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገደሉ

የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ ባወጣው መግለጫ በደቡብ ኦሞ ሱሪ ወረዳ በጉብኝት ላይ የነበሩ ሁለት የውጭ ዜጎችን ጨምሮ ሶስት ሰዎች ተገድለዋል። የተገደሉት ሰዎች ሁለቱ የቱርክ ዜግነት አላቸው የተባለ ሲሆን ሾፌራቸው ደግሞ ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ተገልጿል። ግድያው ትናንት ጠዋት 2:20 ላይ እንደተፈጸመ የተገለጸ ሲሆን የገዳዮቹ ማንነት የአርብቶ አደር ሽፍቶች መሆናቸውን የክልሉ መንግሥት አስታውቋል። ገዳዮቹን በህግ ቁጥጥር ስር ለማዋል የክልሉ ጸጥታ ሀይል እርምጃ መውሰድ ጀምሯልም ተብሏል። ሽፍቶቹ ግድያውን የፈጸሙት ለዝርፊያ በሚል እንደሆነም የክልሉ ኮሙንኬሽን ቢሮ ባወጣው መግለጫ ላይ ጠቅሷል። በርካታ ሀገራት ዜጎቻቸው በኢትዮጵያ ጉብኝት እንዳያደርጉ የጉዞ እገዳ እና ማስጠንቀቂያዎችን ማውጣታቸው ይታወሳል። ለአብነትም ካናዳ እና ብሪታንያ ከወራት በፊት ዜጎቻቸውን ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ አልያም ከተጓዙ በሚል ልዩ…
Read More
በኢትዮጵያ ከተሞች ቢስፋፉም የኑሮ ውድነቱ ፈተና መሆኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከተሞች ቢስፋፉም የኑሮ ውድነቱ ፈተና መሆኑ ተገለጸ

ኢትዮጵያ በያዝነው የ2026 ዓመት የ6.3 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ቢተነበይም፣ በአገሪቱ እየታየ ያለው ፈጣን የከተሞች መስፋፋት በመኖሪያ ቤት፣ በመሠረተ ልማትና በመሠረታዊ አገልግሎቶች ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ሁኔታ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው የከተማ ነዋሪዎች ላይ የኑሮ ውድነትን እያባባሰ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት የከተሞች መስፋፋት የሚታይባት አህጉር ስትሆን፣ የከተማ ነዋሪዎቿ ቁጥር በየዓመቱ ከ3.5 በመቶ በላይ እያደገ ይገኛል። ኢትዮጵያም ለዚህ ፈጣን ዕድገት በምክንያትነት የሚጠቀሱት ከፍተኛ የውልደት መጠን እና ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረግ ፍልሰት ዋነኛ ተዋናይ ናት። ይህ ፍልሰት በመኖሪያ ቤት፣ በመሠረተ ልማትና በመሠረታዊ አገልግሎቶች ላይ ያለውን ፍላጎት በእጅጉ እንዲጨምር አድርጎታል። የፍላጎትና የአቅርቦት አለመመጣጠን ደግሞ የቤት ኪራይንና…
Read More
ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ባለፉት 6 ወራት ከ704 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ ተገለጸ

ኢትዮጵያዊ ባለፉት ስድስት ወራት እንደ ሀገር ከ704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ እንደተቻለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታውቋል።  አፈጻጸሙ በገቢዎች ሚኒስቴር በግማሽ ዓመቱ ለመሰብሰብ ከታቀደው 640 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ውስጥ 704 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የዕቅዱን 110 በመቶ ተሳክቷል ተብሏል። ይህ ገቢ ባለፉት ጊዜያት ለዓመታት ሲሰበሰብ ከነበረው ገቢ ጋር የሚመሳሰል እንደሆነ ተገልጿል። የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ዓመት ስድስት ወራት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ63 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው ሲሆን ስኬቱ ኢትዮጵያ የውስጥ አቅሟን በማጎልበት እያንሰራራች ለመሆኑ ሁነኛ ማሳያ ተድርጎ የሚወሰድ ነው ሲል መንግሥት አስታውቋል። በግማሽ ዓመቱ ከሀገር ውስጥ ታክስ 362 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የተሰበሰበ ሲሆን ከውጪ ንግድ…
Read More
ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን እንዲመሩ ተሾሙ

ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣንን እንዲመሩ ተሾሙ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛው ዓመት የሥራ ዘመን 8ኛው መደበኛ ስብሰባ ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው እንዲሾሙ የቀረበለትን ረቂቅ መርምሮ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል። ምክር ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው የተሿሚዋን የረዥም ዘመን የሙያ ልምድና የሥራ ብቃት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሆኑ ተመልክቷል። ወ/ሮ ሃይማኖት ዘለቀ በመገናኛ ብዙኃንና በኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሰፊ ልምድ ያላቸው ባለሙያ ሲሆኑ በተለይም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከ አርታኢነት በመሥራት ውጤታማ የሥራ ዘመን አሳልፈዋል። በተጨማሪም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) ውስጥ በሙያቸው ያገለገሉ ሲሆን በቀድሞው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤትም በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች አገራቸውን አገልግለዋል። ወደ አሁኑ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ከመምጣታቸው በፊት በአዲስ…
Read More