ኢኮኖሚ

የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ስኩል ስልጠና በድጋሜ ሊጀምር እንደሆነ ተገለጸ

ቲንክ ያንግ (ThinkYoung) እና ቦይንግ (Boeing) ለሁለተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 20ኛው የThinYoung Codeing School ምዝገባ መጀመሩን አስታውቀዋል። መርሃ ግብሩ ከሀምሌ 7 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ. ም የሚካሄድ ሲሆን እድሜያቸው ከ9-18 ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነፃ የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ ትምህርት ይሰጣል ተብሏል። የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ትምህርት ቤት ሥርዓተ ትምህርት በባለሙያዎች የተመቻቹ ሮቦቲክስ እና ሮቦቲከስን  ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን የሚሽፍን ይሆናል። በተጨማሪም የቦይንግ ተወካዮች በአቪዬሽን እና በሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ መስኮች ተነሳሽነትን ለመፍጠር ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች እንደሚያካፍሉ ተገልጿል። እንዲህ ባለው የቲንክ ያንግ እና በቦይንግ አጋርነት በመሰል ኮዲንግ ትምህርት ላይ በተሳተፉ ከ1,300 በላይ ወጣቶች ህይወት ላይ በጎ ተጽዕኖ ያሳድረ ሲሆን በቀደሙት ዙሮች ውስጥ…
Read More
ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

ኢትዮጵያ 50 የኮንስትራክሽን ሰራተኞችን ወደ ጀርመን ልትልክ ነው

በኮንስትራክሽን ሥራ የሚሰማሩ 50 ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ወደ ጀርመን ከማቅናታቸው በፊት አዲስ አበባ ባለው የጀርመን ኢንስቲትዩት ተጨማሪ ስልጠናዎችን በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ በኮንስትራክሽን ሥራ ለመሠማራት የሚያበቃቸውን ሥልጠና ያጠናቀቁ የመጀመሪያው ዙር ባለሙያዎች ወደ ጀርመን እንደሚሄዱ ተገልጿል፡፡ ሥልጠናቸውንና ፈተናቸውን አጠናቀው ጀርመን ከሚገኙ አሠሪዎቻቸው ጋር የሥራ ውል የተፈራረሙት የመጀመሪያዎቹ ተጓዦች በመጪው አንድ ወር ውስጥ  ጉዞ እንደሚያደርጉ ተሰምቷል።  ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በሲቭል ኢንጂነሪንግ፣ በኮንስትራክሽን ማናጅሜንት ቴክኖሎጂ፣ በአርክቴክቸርና መሰል ሙያዎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ምሩቃን ወጣቶች ጎኤቴ በመባል በሚታወቀው የጀርመን ባህልና ቋንቋ ኢንስቲትዩት ሥልጠናቸውን እየተከታተሉ ይገኛሉ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሉት ሥልጠናው ከሦሥት ዓመት በፊት በቀድሞው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር…
Read More
ኢትዮጵያ ለ2016 ነዳጅ ግዢ ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ ለ2016 ነዳጅ ግዢ ከአራት ቢሊዮን ዶላር በላይ እንደሚያስፈልጋት ገለጸች

ኢትዮጵያ በ2016 ዓ.ም 4 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ ከውጭ ለማስገባት ማቀዷን አስታውቃለች። የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት እንዳስታወቀው ለ2016 ዓ/ም ወደ አገር ለማስገባት ለታቀደው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል ። ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋትን ነዳጅ ለማስገባት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ፣ " ቪቶል " የተባለው የባህሬን ኩባንያ በድጋሚ በማሸነፉ የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈርሟል፡፡ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በ2016 ዓ.ም. ለማስገባት ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ቤንዚን፣ እንዲሁም ከጠቅላላው የነጭ ናፍጣ ግዥ 40 በመቶውን " ቪቶል " ኩባንያ እንደሚያስገባ ታውቋል፡፡ በስምምነቱ መሠረት ለ1 ዓመት የሚያስፈልገውን 760 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቤንዚንና 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነጭ ናፍጣ ኩባንያው ያቀርባል ተብላል፡፡…
Read More
ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

ከፊሊፒንስ ጋር የተጣላችው ኩዌት ኢትዮጵያዊያንን እንደምትቀጥር ገለጸች

በነዳጅ የበለጸገችው የመካከለኛው መስራቅ ሀገር ኩዌት የሦስት ወራት አስገዳጅ ስልጠና የወስዱ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ከመንግሥት ጋር ስምምነት ላይ መድረሷ ተገልጿል። በኢትዮጵያ እና ኩዌት መንግሥታት በኩል መግባባት ላይ መደረሱን ተከትሎም፤ በጥቂት ቀናት ውስጥ የጋራ የሥራ ስምምነት እንደሚፈረም አረብ ታይምስ ዘግቧል። ከስምምነቱ በኋላ በኢትዮጵያ የሚገኙ 600 የሚሆኑ የሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሰው ኃይል በማቅረብ ይሰራሉም ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያን ሰራተኞች ቢያንስ ብቃቱ ከተረጋገጠ ተቋም የ3 ወር ስልጠና መውሰድ በግዴታ ተጥሎባቸዋል፡፡ ኩዌት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን የቤት ሰራተኞች የምታገኘው ከፊሊፒንስ ሲሆን፤ በኹለቱ አገራት መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ አገሪቱ የሰራተኛ እጥረት በማጋጠሙ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ለመቀበል ማቀዷ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከኩዌት መንግሥት ጋር በተስማሙት መሰረት፤ አንድ ሰራተኛ በወር 90…
Read More
ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

ኢትዮጵያን የጉዛራ ቤተ መንግሥት በ35 ነጥብ ስምንት ሚሊየን ብር ጥገና ሊደረግለት ነው

በዓለም ቅርስነት የተመዘገበው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው የጉዛራ ቤተመንግሥት ከተደቀነበት የመፍረስ አደጋ ለመታደግ፤ ከፌደራል መንግሥት በተበጀተ 35 ሚሊዮን 800 ሺሕ ብር በጀት የጥገና ሥራው በዛሬው ዕለት እንደሚጀመር ተገልጿል። የጥገና ሥራው በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የጎንደር ዙሪያ ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ፅ/ቤት የቅርስ ጥበቃና ቱሪዝም ልማት ቡድን መሪ ግርማቸው ሙሉጌታ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። ጉዛራ ቤተመንግሥት በጣና ተፋሰስ አካባቢዎች የሚገኝ የመጀመሪያው ቤተመንግሥት እንደሆነ ይነገራል። ጉዛራ ቃሉ የግዕዝ ሲሆን፤ ትርጉሙም ምቹ ማለት ነው። በጎንደር የነገሥታት ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የጉዛራን ቤተመንግሥት የመሰረቱትም ያሳነፁትም ኢትዮጵያን ከ1556-1589 ድረስ በመሩት በአፄ ሰርፀ ድንግል መሆናቸው በፁሁፍ የሰፈሩ ማስረጃዎች ያሳያሉ። የጉዛራ ቤተመንግሥት ከእንፍራንዝ በስተደቡብ 5 ኪሎሜትር ወጣ ብሎ የተሰራ…
Read More
በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ሁዋዌ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ባካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተወዳደሩት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች የተሳተፉ  ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎች  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ ሴኪዩሪቲ፣ WLAN፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ AI፣ OpenEuler እና OpenGaussን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ  ተሳትፈዋል። በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች የራሳቸውን የፈጠራ ሃሳብ ይዘው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎቹ “የግእዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ መወዳደሪያ ይዘው ቀርበዋል፡፡ የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ…
Read More
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ሊገዙ ነው

ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ሊገዙ ነው

የአፍሪካ ቁጥር አንድ ባለጸጋው ናይጀሪያዊው አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ለመግዛት እንደሚፈልጉ ተገልጿል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከአንድ ዓመት በፊት በይዞታው ስር ያሉ የስኳር ፋብሪካዎችን መሸጥ እንደሚፈልግ መግለጹ ይታወሳል። በዚህ መሰረትም የስኳር ፋብሪካዎችን የመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦች እና ተቋማት ፍላጎታቸውን እንዲያሳውቁ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ናይጀሪያዊው የአፍሪካ ቀዳሚ ቢሊየነር ፍላጎታቸውን ከገለጹ ባለሀብቶች መካከል አንዱ መሆናቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ፋብሪካ ያላቸው አሊኮ ዳንጎቴ አሁን ደግሞ የስኳር ፋብሪካ የመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ተገልጿል። ከአሊኮ ዳንጎቴ በተጨማሪም ኮካ ኮላ ኩብንያም በኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካ ለመግዛት ከሚፈልጉ የቢዝነስ ተቋማት መካከል አንዱ ነው ተብሏል። የገንዘብ ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ሰዎች በዚህ ሳምንት የስኳር ፋብሪካዎቹን ጨረታ በተመለከተ በሰጡት መግለጫ…
Read More
ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ

ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ

ሩሲያ እና ቻይና አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቻቸው ለማስተማር ወሰኑ የዓለማችን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ እና ብዙ ህዝብ ያላቸው ሩሲያ እና ቻይና የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ የሆነው አማርኛ ቋንቋ ለዜጎቻቸው እንዲሰጥ መወሰናቸውን አስታውቀዋል፡፡ ሩሲያ ከቀጣዩ መስከረም ወር ጀምሮ በሞስኮ በሚገኙ አራት ትምህርት ቤቶች ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጻለች፡፡ ትምህርቱ ከቀጣዩ መስከረም 2016 ዓ.ም ጀምሮ ይሰጣል የተባለ ሲሆን በሳምንት ሁለት ክፍለ ጊዜ እንደሚሰጥ በሞስኮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የእስያ እና አፍሪካ ጥናት ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር አሌክሲ ማስሎቭ ገልጸዋል፡፡ ሌላኛዋ አማርኛ ቋንቋን ለዜጎቿ ለማስተማር የወሰነችው ሀገር ቻይና ስትሆን ትምህርቱ በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) ከሚሰጡ 101 የውጭ ቋንቋ ትምህርቶች አንዱ ይሆናል ተብሏል፡፡ ለዚህ እንዲረዳም አማርኛን ለቻይናዊያን ተማሪዎች ለማስተማር የሚያግዘው መጽሀፍ በቤጂንግ…
Read More
የአዲስ አበባ የ70 ዓመት ባለውለታ አረፉ

የአዲስ አበባ የ70 ዓመት ባለውለታ አረፉ

በአዲስ አበባ ከተማ ላለፉት 70 ዓመት ዳቦ በማቅረብ የሚታወቁት የ'ሸዋ ዳቦ' መሥራቹ ዘሙይ ተክሉ ማረፋቸው ተሰምቷል። የአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ሥያሜውን የተዋሱት የሸዋ ዳቦ መሥራቹ አቶ ዘሙይ ተክሉ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል። የኤርትራ መሠረት ያላቸው ዘሙይ ወደ አዲስ አበባ ዘልቀው ያቋቋሙት ሸዋ ዳቦ ለ70 ዓመታት ለአዲስ አበቤዎች ዳቦ ሲያቀርብ ቆይቷል። የአምስት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ዘሙይ አንደኛዋ ልጃቸው በአዲስ አበባ ሥማቸው ከሚጠራ ኬክ ቤቶች መካከል የሆነው የ'ቤሎስ ኬክ' ቤት መስራች ሆናለች። በደርግ አስተዳድር ዘመን ለኤርትራ መገንጠል የሚዋጉ አማጽያንን በመደገፍ ታስረው የነበሩት ዘሙይ ተክሉ፣ በከተማዋ የሌላኛው ሥመ ጥር ኬክ ቤት መሥራች የበላይ ተክሉ ወንድምም ናቸው። ሸዋ ዳቦ ቤት በስንዴ መወደድ…
Read More
ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

የቻይናዋ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሼንዘን ከተማ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድርን ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ታስተናግዳለች፡፡ በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች ወደ ቻይና ያቀኑ ሲሆን ለተወዳዳሪዎቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡ ውድድሩን ህዋዌ ያዘጋጀው ሲሆን በየሀገሩ በተካሄደ የማጣሪያ ውድድሮች ላይ አሸናፊ የሆኑ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ተማሪዎቹ በዚህ  ዓለም አቅፍ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ያቀኑት የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳትፈው በየደረጃው በአሸናፊነት በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያን በዚህ ውድድር ላይ የወከሉት ዘጠኙ ተማሪዎች  የተገኙት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች ነው። በውድድሩ ተማሪዎቹ  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን…
Read More