07
Jun
ቲንክ ያንግ (ThinkYoung) እና ቦይንግ (Boeing) ለሁለተኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው 20ኛው የThinYoung Codeing School ምዝገባ መጀመሩን አስታውቀዋል። መርሃ ግብሩ ከሀምሌ 7 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ. ም የሚካሄድ ሲሆን እድሜያቸው ከ9-18 ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነፃ የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ ትምህርት ይሰጣል ተብሏል። የቲንክ ያንግ ኮዲንግ ትምህርት ቤት ሥርዓተ ትምህርት በባለሙያዎች የተመቻቹ ሮቦቲክስ እና ሮቦቲከስን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን የሚሽፍን ይሆናል። በተጨማሪም የቦይንግ ተወካዮች በአቪዬሽን እና በሌሎች የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሒሳብ መስኮች ተነሳሽነትን ለመፍጠር ልምዳቸውን ለተሳታፊዎች እንደሚያካፍሉ ተገልጿል። እንዲህ ባለው የቲንክ ያንግ እና በቦይንግ አጋርነት በመሰል ኮዲንግ ትምህርት ላይ በተሳተፉ ከ1,300 በላይ ወጣቶች ህይወት ላይ በጎ ተጽዕኖ ያሳድረ ሲሆን በቀደሙት ዙሮች ውስጥ…