Anwarsoussa

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊ ተሾመለት። ላለፉት ሁለት ዓመታት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በሀላፊነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ መልቀቃቸው ይታወሳል። ድርጅቱ ባሳለፍነው ሳምንት እንዳለው አንዋር ሶሳ ከቀጣዩ ወር ጀምሮ በሀላፊነታቸው እንደማይቀጥሉ አስታውቋል። ይህን ተከትሎም የቀድሞው የኤምቲኤን ኡጋንዳ ሀላፊ የነበሩት ዊም ቫንሄልፑት አንዋር ሶሳን ተክተው ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ሮይተርስ ዘግቧል። በዜግነት ቤልጂየማዊ የሆኑት አዲስ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ ድርጅቱን መምራት ይጀምራሉ። ሳፋሪሎም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የሆኑት ሔኖክ ተፈራን የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮ ቴሌሎም ብርቱ…
Read More
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ አንዋር ሶሳ ከሓላፊነት ለቀቁ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት ዓለም አቀፍ ጨረታ ማሸነፉን ተከትሎ ነበር አንዋር ሶሳ ወደ አዲስ አበባ የመጡት። ከ2019 ጀምሮ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ አሁን ላይ ከሀላፊነት መነሳታቸውን ድርጅታቸው አስታውቋል። ይሁንና ሳፋሪኮም ለምን አንዋር ሶሳን ከሀላፊነት እንዳነሳቸው እስካሁን ይፋ አላደረገም። ከአንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎቶችን መስጠት የጀመረው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአጭር ወራት ውስጥ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን እንዳፈራ አስታውቋል። የኔትወርክ አገልግሎቶችን ከኢትዮ ቴሌኮም በመከራየት ደንበኞችን እያገለገለ የሚገኘው ሳፋሪ ኮም የኢትዮጵያ ገበያው ያሰበውን ያህል እንዳልሆነለት ከዚህ በፊት መግለጹ አይዘነጋም። ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ አምባሳደር ሔኖክ ተፈራን መሾሙ ይታወሳል። ላለፉት ሶስት…
Read More