መነሻ ገፅ

በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ወደ አራት ክልሎች ተዛመተ

በኢትዮጵያ የኮሌራ ወረርሽኝ ወደ አራት ክልሎች ተዛመተ

በሳሙኤል አባተ የኮሌራ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች መዛመቱን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። በደቡብ ክልል ልዩ ልዩ ዞኖች እና ወረዳዎች ደግሞ በወረርሽኙ ከተጠቁ 920 ሰዎች መካከል የ18 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል። የጤና ጥበቃ ሚንስቴርም ወረርሽኙ በተስፋፋባቸው አካባቢዎች ክትባት መስጠት ተጀምሯል። በኢትዮጵያ፣ የኮሌራ ወረርሽኝ፣ በአራት ክልሎች መዛመቱን ያስታወቀው የጤና ሚኒስቴር፣ ወረርሽኙን ለመከላከል፣ ለ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ዜጎች ክትባት እንደሚሰጥ አመልክቷል፡፡ በኢትዮጵያ አራት ክልሎች ተዛምቶ ጉዳት እያደረሰ የሚገኘው ይህ ወረርሽኝ በዐዲስ መልክ በተከሠተባቸው የደቡብ ክልል አምስት ዞኖች እና ሦስት ልዩ ወረዳዎች ተስፋፍቷል ተብሏል። የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ወረርሽኙ፥ በአገር አቀፍ ደረጃ በአራት ክልሎች መከሠቱን አረጋግጠዋል። ወረርሽኙ ከተስፋፋባቸው ክልሎች መካከልም ኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሊ…
Read More
ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተርሚላን ለአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ አለፉ

በአውሮፓ ምርጥ እግር ኳስ ክለቦች ሙካከል ሲካሄድ የቆየው የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ተፋላሚዎች ታውቀዋል። ትናንት ምሽት በእንግሊዝ ማንችስተር ከተማ በሪያል ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ መካከል የተካሄደው ውድድር በሲቲ የበላይነት ተጠናቋል። በርናርዶ ሲልቫ ሁለት ጎል፣ አልቫሬዝ እና ሚሊታኦ በራሱ ግብ ላይ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ሲቲ በቱርክ ኢስታምቡል ከተማ ለሚካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማለፍ ችሏል። የጣልያኑ ኢንተር ሚላን በፍጻሜው ማንችስተር ሲቲን የሚገጥም ሲሆን ጨዋታው ሰኔ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት 4:00 ላይ ይካሄዳል ተብሏል። የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ውድድርን የስፔኑ ሪያል ማድሪድ 14 ጊዜ በማሸነፍ ቀድሚው ክለብ ሆኖ ተመዝግቧል። የፍጻሜ ተፋላሚው ማንችስተር ሲቲ እስካሁን አንድም ጊዜ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግን ያላሸነፈ ሲሆን ሌላኛው የፍጻሜ ተፋላሚ ኢንተርሚላን ሶስት…
Read More
በኢትዮጵያ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች የረሀብ አድማ ጀመሩ

በኢትዮጵያ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች የረሀብ አድማ ጀመሩ

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞች እና ምሁራን የረሃብ አድማ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። መንግሥትን በኃይል ለመጣል አሲረዋል በሚል የሽብርተኝነት ክስ ቀርቦባቸው በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች እና ምሁራን የረሃብ አድማ ላይ መሆናቸውን የእስረኞቹ ቤተሰቦች ገለጹ። ተጠርጣሪዎቹ የረሃብ አድማውን የጀመሩት ከትላንት ጀምሮ ሲሆን፤ አድማው ለሦስት ተከታታይ ቀን የሚቆይ እንንደሆነ ተገልጿል። የረሃብ አድማው ላይ ከሚገኙት እስረኞች መካከል ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሳሳይ፣ መምህርት መስከረም አበራ፣ ረዳት ፕ/ር ሲሳይ አውግቸው፣ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ እና ሌሎች የሽብር ክስ የቀረበባቸው ታሳሪዎች ይገኙበታል። የአድማው ምክንያት ከእነሱ እስር በተጨማሪ በምንም ጉዳይ ላይ ተሳትፎ የሌላቸው ሰዎች በብዛት የሚታሰሩበትን ሁኔታ ለመቃወም ነውም ተብሏል። የፌደራል መንግሥት ጸጥታ እና ደኅንነት የጋራ…
Read More
የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

የአዳማ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ሚሊዮን ብር ሽልማት አሸነፉ

አቢሲኒያ ባንክ ለሶስት እንስቶች አንድ ሚሊዮን ብር ሸለመ ባንኩ "አሚን አዋርድ" በሚል የሰየመውን የሥራ ፈጠራ ውድድር አጠናቋል፡፡ ውድድሩ ካሳለፍነው ህዳር ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ በሥራ ፈጠራቸው ይዘት እና ችግር ፈቺነታቸው ለተመረጡ 5 ተወዳዳሪዎች የእውቅናና የሽልማት መርሐ-ግብር በአዳማ ከተማ ተካሂዷል፡፡ በውድድሩ ላይ ከ1ኛ - 5ኛ ለወጡ ተሳታፊዎች በአጠቃላይ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የተሸለሙ ሲሆን ከ6ተኛ እስከ 20ኛ ድረስ ለወጡ ተሳታፊዎችም የማበረታቻ ሽልማት መሰጠቱን አቢሲኒያ ባንክ ለኢትዮ ነጋሪ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡ የአንደኝነት ደረጃን በማግኘት የ1,000,000 ብር ተሸላሚ የሆኑት በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩ ሦስት እንስቶች አሸንፈዋል፡፡ እንስቶቹ ‹ግሪን ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ማዳበሪያ› በሚል በጋራ ባቋቋሙት ድርጅት ስም አሸናፊ በመሆን ሽልማቱ ተበርክቶላቸዋል፡፡
Read More
ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለሽያጭ አቀረበ

ደርጅቱ በቀጣዮቹ አምስት አመታት ውስጥ 10 ሺህ ቤቶችን እንደሚገነባ አስታውቋል፡፡ ከ30 አመታት በላይ በመኖሪያ ቤት ግንባታ እና በኮንስትራክሽን ዘርፉ የተሰማራዉ ፍሊንትስቶን ሪልስቴት 10 ሚሊዮን አክሲዮኖችን ለገበያ ማቅረቡን አስታዉቋል። የፍሊንትስቶን መስራችና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጸደቀ ይሁኔ እንደተናገሩት ከ20 ሺህ ብር ጀምሮ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ድረስ ዋጋ ያላቸዉን አክሲዮኖች ለሽያጭ መቅረባቸዉን ተናግረዋል። የአንዱ አክሲዮን ዋጋም 1 ሺህ ብር መሆኑን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ከሚቀጥለው ሐምሌ ጀምሮ ሽያጩ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ባለ አክሲዮኖች ባላቸዉ የድርሻ መጠን ተሰልቶ አልያም በፍላጎታቸዉ ተጨማሪ ገንዘብ ከፍለዉ የቤት ባለቤት መሆን የሚችሉበት እድል መመቻቸቱን ገልጸዋል፡፡ በዋነኛነት አክሲዮን ሽያጩ ያስፈለገዉ ተጨማሪ ካፒታል ለማግኘት ፣ ድርጅቱን ከ አምስት ሰዎች የሽርክና ባለቤትነት…
Read More
ህወሓት የምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሕልውናዬን የሚያከስም በመሆኑ አልቀበለውም አለ

ህወሓት የምርጫ ቦርድ ውሳኔ ሕልውናዬን የሚያከስም በመሆኑ አልቀበለውም አለ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሰሞኑ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ጉዳይ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡ ቦርዱ ከዚህ በፊት ህወሓት ከምርጫ ቦርድ እውቅና ውጪ ምርጫ በማድረጉ፣ ወደ ትጥቅ ትግል እና አመጽ ተግባር ገብቷል በሚል ፓርቲው እንዲከስም ውሳኔ አስተላልፎ ነበር፡፡ ህወሓት ለምርጫ ቦርድ ባስገባው ማመልከቻ ጦርነቱ በሰላም ስምምነት መጠናቀቁን ተከትሎ እና ከሽብርተኝነት መሰረዙን ተከትሎ  በምርጫ ቦርድ የተላለፈብኝ ውሳኔ ይነሳልኝ ሲል አመልክቶ ነበር፡፡ ምርጫ ቦርድም ከዚህ በፊት በህወሓት ላይ ያስተላለፍኩት ውሳኔን መቀልበስ የምችልበት ህጋዊ አሰራር የለም ሲል ምላሽ ሰጥቶም ነበር፡፡ ይህንን ተከትሎም ህወሓት ከቀናት በፊት ምርጫ ቦርድ ያሳለፈውን ውሳኔ እንደማይቀበለው ባወጣው መግለጫ አሳውቋል። የምርጫ ቦርድን ውሳኔ " አልቀበለውም " ያለው ህወሓት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር…
Read More
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ተሾመ

ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ተሾመ

ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝ ሆነው መሾማቸው ተገልጿል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑን በጊዜያዊነት የሚመሩ አሰልጣኞችን ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ብሔራዊ ቡድኑን ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲመሩ ከቆዩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ጋር በስምምነት ከተለያየ በኋላ ቀጣዩን አሰልጣኝ ለመምረጥ የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውይይት ማድረጉን ገልጿል። በዚሁ መሰረት ኮሚቴው በቴክኒክ ዳይሬክተርነት እየሰሩ የሚገኙትን ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት ቀጣይ ጨዋታዎችን እንዲመሩ ከውሳኔ ላይ መድረሱን አመልክቷል። በተጨማሪ ኮሚቴው ኢንስትራክተር ዳንኤልን እንዲያግዙ በፕሪምየር ሊጉ በመስራት ላይ የሚገኙትና በወቅታዊ ውጤታማነት የተሻሉ ሆነው ተገኝተዋል ያላቸውን የባህር ዳር ከተማ አሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛው ምክትል አሰልጣኝ ሆነው እንዲሰሩ መወሰኑን ጠቅሷል። ፌዴሬሽኑ…
Read More
የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ

የኢትዮጵያ የውጭ እዳ 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ። ኢትዮጵያ ከአገር ውስጥ ባንኮች የተበደረችውን ሳይጨምር ከውጭ አበዳሪ ምንጮች ተበድራ ያልመለሰችው የዕዳ መጠን 28 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የገንዘብ ሚንስቴር አስታውቋል። እንደ ሚኒስቴሩ ሪፖርት ከሆነ ኢትዮጵያ ካለባት 28 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ውስጥ 54 በመቶ የተገኘው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት ባንክ ነው፡፡ 46 በመቶው ደግሞ ከቻይና እና ከሌሎች ውጭ የግል አበዳሪ ተቋማት የተገኘ እንደሆነ ተገልጿል። ኢትዮጵያ ባለባት ከፍተኛ የውጭ ዕዳ ብድር ምክንያትም በዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት ምደባ ከፍተኛ የዕዳ ጫና ያለባቸው አገሮች ዝርዝር ውስጥ ተመድባለች። በተያያዘ ዜና ኢትዮጵያ ከሶስት ዓመት በፊት የቡድን 20 አገሮች የዕዳ ጫናን ለማቅለል ባዘጋጁት የዕዳ መልሶ ማዋቀር ሥርዓት ለመጠቀም…
Read More
ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ደቡብ ኮሪያ በኢትዮጵያ ግብርናን ለማዘመን 10 ሚሊዮን ዶላር ለገሰች

ኢትዮጵያ እና የኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ የ10 ሚሊየን ዶላር የድጋፍ ስምምነትን በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል። የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እና በኢትዮጵያ የኮይካ ሃላፊ ሊ ቢዩንግህዋ ፈርመውታል። የገንዘብ ድጋፉ የኢትዮጵያን ግብርና ለማዘመን ይውላል የተባለ ሲሆን በተለይም የወተት እና የወተት ተዋጽኦ ምርታማነትን ለማሳደግ ያስችላል ተብሏል። የወተት ምርታማነትን የሚያሳድገው ይህ ፕሮጀክት በቀጣዮቹ ስድስት ዓመታት እንደሚተገበር የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሮጄክቱ በወተት ልማት እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን መደገፍ ላይ ትኩረቱን እንደሚያደርግም ተገልጿል። የተሻሻሉ የወተት ላሞችን ለአርሶ አደሩ ማቅረብ፣ የወተት ምርታማነትን መጨመር፣ በማህበር የተደራጁ ወተት አቅራቢዎችን የገበያ እድሎችን ማስፋት፣ ተጨማሪ ሌሎች አሰራሮችን መዘርጋት የፕሮጀክቱ ዓላማ ነው ተብሏል።…
Read More
በሰርግ ላይ በተተኮሰ ጥይት ሙሽራው እና አባትየው ተገደሉ

በሰርግ ላይ በተተኮሰ ጥይት ሙሽራው እና አባትየው ተገደሉ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን በቋሪት ወረዳ ወይበኝ ቀበሌ ልዩ ቦታው በተለምዶ አነሳት እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ በተዘጋጀ ሰርግ ላይ የሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል። በባህሉ በወጉ መሰረት ልጃችንን ለልጃችሁ ተባብለው ሙሽሪትና ሙሽራው ሊጣመሩ የሙሽራው ቤተሰብና የሙሽሪት ቤተሰብ በስጋ ዝምድና ሊጣመሩ ቤት ባፈራው እንደአቅም ድግስ በመደገስ የሩቁና የቅርቡ ወዳጅ ዘመድ ልጃችንን ስለምንድር ልጃችንን መርቁልን ማለት የተለመደ ስርዓትና ወግ ነው፡፡ በትናንትናው ዕለት ማለትም ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ለሰርጉ ድምቀት የተጠራው ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ወደ ቤታቸው ሊወጡ ሲሉ የደስ ደስ ጥይት ይተኮሳል። በዚህ ሰዓትም በተተኮስ ጥይት ሙሽራው እና የሙሽራው አባት ወዲያውኑ ህይታቸው ማለፉ ተገልጿል። እንዲሁም አንድ የሴት ሚዜ አና ሰርጉን ለማድመቅ የተገኙ 4…
Read More