Gojam

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ጅጋ ከተማ 18 ሰዎች በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ተገደሉ

የጸጥታ ሀይሎቹ የአዕምሮ ህመምተኛን ጨምሮ በመዝናናት ላይ የነበሩ የባንክ ሰራተኞችን እና መምህራንን ገድለዋል በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ጅጋ ከተማ፤ ቢያንስ 18 ሰዎች “በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን” ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ብሔራዊው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፤ “በአካባቢው ጥቃት ተፈጽሟል” የሚል መረጃ እንደደረሰው ገልጾ ፤ ክስተቱን እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። የዓይን እማኞቹ፤ የጅጋ ከተማ ነዋሪዎች የተገደሉበት ክስተት የተፈጸመው ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 9፤ 2016 አመሻሽ ላይ መሆኑን ገልጸዋል። በዚሁ ዕለት ምሽት 11 ሰዓት ገደማ፤ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን የጫኑ “ሶስት ፓትሮል” ተሽከርካሪዎች ከደንበጫ ወደ ጅጋ ከተማ እየገቡ በነበረበት ወቅት፤ “በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አባላት” ከፊት በነበረው መኪና ላይ ጥቃት ካደረሱ በኋላ መሸሻቸውን የዓይን እማኞቹ አብራርተዋል። ጥቃት…
Read More
በአማራ ክልል ጎጃም ሰከላ 40 ንጹሃን ነዋሪዎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ጎጃም ሰከላ 40 ንጹሃን ነዋሪዎች ተገደሉ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን ሰከላ ከግንቦት 5 እስከ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ 40 ሰዎች ተገድለዋል ተብሏል፡፡ የመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ንጹሃኑን የገደሉት ወደ ቤተክርስቲያን ሲሄዱ የነበሩ እና የሰርግ ስነስርዓትን ታድመው ሲመለሱ እንደሆነ አሻም ቲቪ ዘግቧል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች እና የተጎጂ ቤተሰቦች እንዳሉት በአካባቢው ከዚህ ቀደም ብሎ ግንቦት 4 በፋኖ ሀይሎች እና በመከላከያ ሰራዊት መካከል ውጊያ እንደነበር ተናግረዋል። የአካባቢው ነዋሪዎችም በስጋት ምክንያት አካባቢያቸውን ለቀው ወደ ባህርዳር እና ወደ ሌሎች ገጠራማ አካባቢዎች መሰደዳቸውን ተናግረዋል። የምዕራብ ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት ምክትል ሰብሳቢ አቶ እድሜአለም አንተነህ በበኩላቸው በአካባቢው ውጊያ እንደነበር ገልፀው ነገርግን አንድም ንፁሃን አልተገደለም ማለታቸውን በዘገባው ላይ ተጠቅሷል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት በአማራ…
Read More
በሰርግ ላይ በተተኮሰ ጥይት ሙሽራው እና አባትየው ተገደሉ

በሰርግ ላይ በተተኮሰ ጥይት ሙሽራው እና አባትየው ተገደሉ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን በቋሪት ወረዳ ወይበኝ ቀበሌ ልዩ ቦታው በተለምዶ አነሳት እየተባለ ከሚጠራው ስፍራ በተዘጋጀ ሰርግ ላይ የሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል። በባህሉ በወጉ መሰረት ልጃችንን ለልጃችሁ ተባብለው ሙሽሪትና ሙሽራው ሊጣመሩ የሙሽራው ቤተሰብና የሙሽሪት ቤተሰብ በስጋ ዝምድና ሊጣመሩ ቤት ባፈራው እንደአቅም ድግስ በመደገስ የሩቁና የቅርቡ ወዳጅ ዘመድ ልጃችንን ስለምንድር ልጃችንን መርቁልን ማለት የተለመደ ስርዓትና ወግ ነው፡፡ በትናንትናው ዕለት ማለትም ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ለሰርጉ ድምቀት የተጠራው ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ወደ ቤታቸው ሊወጡ ሲሉ የደስ ደስ ጥይት ይተኮሳል። በዚህ ሰዓትም በተተኮስ ጥይት ሙሽራው እና የሙሽራው አባት ወዲያውኑ ህይታቸው ማለፉ ተገልጿል። እንዲሁም አንድ የሴት ሚዜ አና ሰርጉን ለማድመቅ የተገኙ 4…
Read More