Blog

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነገ ፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ይሰጣሉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በነገው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፌዴራል መንግሥት የ2015 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ምክር ቤቱአስታውቋል። የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 28ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ሰኔ 29/2015 ያካሂዳል፡፡ ምክር ቤቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ2016 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን አስመልክቶ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ የበጀት አዋጁን ያጸድቃል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት ለጠቅላይ ሚንስትሩ ጥያቄ እንደሚያቀርቡ የሚጠበቅ ሲሆን በተለይም ከዜጎች ደህንነት ጋር በተያያዘ ብዙ ጥያቄ እንደሚቀርብላቸው ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ከሶስት ወራት…
Read More
ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ለምርጫ ስርዓት ማጠናከሪያ የ30 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አገኘች

ኢትዮጵያ ዘላቂ ዲሞክራሲን ለማስፈን የሚያስችላትን የምርጫ ስርአት እንድታጠናክር ለማግዝ የሚውል የ30 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዶላር የፋናንስ ድጋፍ ስምምነት ፈርማለች፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስቴር፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት መካካል ተፈርሟል፡፡ የበጀት ድጋፉ የምርጫ ቦርድ ተቋማዊ መዋቅርን ለማጠናከር ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ አሳታፊ ፣ተአማኒና ደረጃውን የጠበቀ ምርጫና ህዝበ ውሳኔ እንዲያካሂድ ተቋሙን ማጠናከር፣ ከሲቪክ ተቋማት በጋራ በመሆን በምርጫ ሂደት የሴቶችና ወጣቶች ተሳትፎን ለማሳደግ ይውላል ተብሏል፡፡ እንዲሁም የበጀት ድጋፉ በኢትዮጵያ ነፃ ፍትሀዊ እና ተአማኒ ምርጫ እንዲያከሂድ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንደሚውልም የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ይህ የበጀት ድጋፍ ፕሮጀክት በሚቀጥሉት አራት አመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን የሀገሪቱን የምርጫ ስርአት በማጠናከር ዘላቂ ዴሞክራሲን ለማስፈን አስተዋጽኦ…
Read More
ትምህርት ሚኒስቴር የሬሚዲያል ፈተናዎችን ሰረዘ

ትምህርት ሚኒስቴር የሬሚዲያል ፈተናዎችን ሰረዘ

የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን ወስደው ወደ ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን የሬሚዲያል ፕሮግራም በመስጠት ለይ መሆኑ ይታወሳል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከትናንት ሰኔ 26 ቀን ጀምሮ የ12ኛ ክፍል ፈተናን በያሉበት ሆነው በመፈተን ላይ ናቸው፡፡ ይሁንና ሚኒስቴሩ ይህ ፈተና መሰረዙን ያስታወቀ ሲሆን ምክንያቹን ከመናገር ተቆጥቧል፡፡ በፈተና ሂደት በተፈጠሩ ችግሮች ምክንያት የትምህርት ሚኒስቴር ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ.ም የተሰጡት የሬሜዲያል ፕሮግራም ፈተናዎች ተሰርዘው ተማሪዎች በቀሩት የትምህርት ዓይነቶች ብቻ እንዲመዘኑ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ እንዲሁም ቀደም ብሎ በሁሉም ሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ተማሪዎች ባላቸው ተቋማት ፈተናውን በአንድ ጊዜ ለመስጠት የታቀደው ፕሮግራም ማሻሻያ እንደተደረገበትም ገልጿል፡፡ በተለይም ከ150 በላይ የሆኑና ከ200 በላይ ካምፓስ ያላቸውን…
Read More
ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከሞባይል ክፍያ ሥርዓት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ የማግኘት አቅም እንዳላት ተገለጸ

በኢትዮጵያ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት በስፋት ጥቅም ላይ ከዋለ የአገር ዉስጥ እድገት 5 ነጥብ 3 ቢሊዮን ዶላር እንደሚጨምር ዓለም አቀፍ የሞባይል ግንኙነት ስርዓት ማኅበር አስታውቋል። ይህም የሚሆነው በፈረንጆች 2030 ከአጠቃላይ የአገሪቱ ሕዝብ 60 በመቶ ያህሉ የሞባይል ክፍያ ሥርዓት ተጠቃሚ ከሆኑ ነው ያለው ማኅበሩ፤ በተጨማሪም 700 ሺሕ ሰዎችን ከአስከፊ ድህነት እንደሚያወጣና የታክስ ገቢን በ300 ሚሊዮን ዶላር እንደሚጨምር አመላክቷል፡፡ ይሁን እንጂ በኢትዮጵያ በአንፃራዊነት 99 በመቶ የኔትወርክ ሽፋን ተደራሽነት ቢኖርም፤ የኔትዎርክ ጥራት አስተማማኝ አለመሆን፣ የዲጂታል ስርዓቱ ግንዛቤ ጉድለት፣ የዕምነትና የመረጃ ግላዊነትና ደህንነት ጥያቄ እንዲሁም የግብይቶች በተደጋጋሚ መስተጓጎል የሞባይል ገንዘብ ክፍያን እና አጠቃቀም ላይ እንቅፋት እየሆነ እንደሚገኝ ተጠቅሷል። በተጨማሪም በ2021 የኤሌክትሪክ ኃይል ያላቸው ኢትዮጵያውያን 51…
Read More
የደጀን ከተማ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው ተገደሉ

የደጀን ከተማ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው ተገደሉ

በአማራ ክልል፤ የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው “በግለሰብ በተፈጸመባቸው ጥቃት” ህይወታቸው አለፈ። በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን የምትገኘው የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ እና ምክትላቸው በተከፈተባቸው ተኩስ ሲገደሉ ሁለት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል። ለወረዳዋ ፖሊስ አዛዦች ህልፈት ምክንያት የሆነውን ተኩስ ከፍቷል የተባለ ተጠርጣሪን ለመያዝ ፍለጋ እየተከናወነ መሆኑንም ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። የደጀን ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ዘውዱ ታደለ እና ምክትላቸው ኢንስፔክተር ወርቁ ሽመልስ ጥቃት የተፈጸመባቸው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 26፤ 2015 ከቀኑ ስምንት ሰዓት ገደማ እንደሆነ የወረዳው የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታሁን ጋሻዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የፖሊስ አዛዦቹ ላይ ተኩስ የተከፈተባቸው፤ በዛሬው ዕለት በተለያዩ አካባቢዎች…
Read More
አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

አዲስ አበባ የሩሲያዊ ደራሲ አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሐውልት ዳግም ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ የታዋቂውን ሩሲያዊ ደራሲ ፑሽኪን ሐውልትን ወደ አደባባይ ልትመልስ መሆኗን ገለጸች የሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በፈረንጆቹ 2002 ላይ ነበር የታዋቂውን የሩሲያዊ የስነ ጽሁፍ ሰው አሌክሳንደር ፑሽኪንን ሀውልት በስጦታ መልኩ ለአዲስ አበባ የሰጠችው። ይህ ሀውልት ለረጅም ዓመታት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ስር ባለ አንድ አደባባይን የፑሽኪን አደባባይ በሚል የሰየመችው። በዚህ አደባባይ ላይም የፑሽኪን ሐውልት ተተክሎ የቆየ ቢሆንም የትራፊክ መጨናነቅን ለማስቀረት በሚል አደባባዩ ፈርሷል። የአሌክሳንደር ፑሽኪን ሀውልትም ወደ ኢትዮጵያ ሙዚየም ግቢ ውስጥ እንዲቀመጥ ተደርጎ ቆይቷል። የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ለአልዐይን እንዳሉት የፑሽኪን ሀውልት ወደ አደባባይ ወጥቶ ይተከላል ብለዋል። "ሀውልቱ የሩሲያን እና ኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትን ክብር…
Read More
የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በቅርቡ የጀመረው አድማስ ድጅታል ሎተሪ የሽልማት መጠኑን ማሳደጉን ገልጿል፡፡ አድማስ ድጅታል ሎተሪ ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንደኛ አሸናፊ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በመሸለም ነበር የጀመረው፡፡ በመቀጠልም የሽልማት መጠኑን ወደ ሶስት ሚሊዮን ብር ከፍ የተደረገው አድማስ ድጅታል ሎተሪ ደንበኞች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም በሶስት ብር እና በአምስት ብር የሎተሪ እጣ የሚቆርጡበት የሎተሪ ስርዓት ነው፡፡ በደምበኞች አስተያየት መሰረት ቀደም ሲል የነበበረውን የዕጣ ሽልማት የአንደኛው ዕጣ 4 ሚሊዮን ብር፣ የሁለተኛው ዕጣ 2 ሚሊዮን ብር የሶስተኛው ዕጣ 1 ሚሊዮን ብር በማድረግ ተደርጓል ተብሏል፡፡ እንዲሁም ደንበኞች ከሰኔ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አንድ እጣ በ10 ብር በ605 ላይ ማንኛውም ፊደል በመላክ…
Read More
ፓስተር ዮናታን የ77 ሚሊዮን ብር የባንክ እዳ እንዳለባቸው ተገለጸ

ፓስተር ዮናታን የ77 ሚሊዮን ብር የባንክ እዳ እንዳለባቸው ተገለጸ

በፓስተር ዮናታን ንብረቶች ላይ ንብ ባንክ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ አወጣ። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ላበደረው ንብረት የሐራጅ ሽያጭ አውጥቷል። ንብ ባንክ በሰኔ 22 ቀን የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ባስወጣው የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ መሰረት በአዲስ አበባ እና ሀዋሳ ባሉ የመኖሪያ ቤት እና ንግድ ድርጅቶችን ለመሸጥ ለተጫራጮች ማስታወቂያ አውጥቷል። አበዳሪው ወይም የመያዢያ ሰጪ ስም፣ አበዳሪው ቅርንጫፍ፣ የሚሸጠው ንብረት ዓይነትና የሚገኝበት ቦታ፣ የሐራጁ መነሻ በብር፣ የሐራጁ ቀንና ሰዓትም ተገልጿል። ጨረታ ከወጣባቸው ንብረቶች መካለም አቶ ዮናታን አኪሊሉ አንጀሎ አራት ኪሎ ፕሪሚየም፣ በስማቸው የተመዘገበ ሀዋሳ ምሥራቅ ከተማ የሚገኝ 400 ሜትር ካሬ ቦታ ያለው ባለ 3 ወለል መኖሪያ ቤት ሲሆን የሐራጁ መነሻ ዋጋ 22 ሚሊዮን ብር…
Read More
በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 200 ሺህ ዜጎች መሞታቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 200 ሺህ ዜጎች መሞታቸው ተገለጸ

በፈረንጆች 2022 ብቻ በኢትዮጵያ በረሃብና በበሽታ ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ በፈረንጆቹ 2022 ዓመት ብቻ በኢትዮጵያ በረሃብ እና ከረሀብ ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ በሽታዎች በተያያዘ ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉ ተገልጿል። በዚህም በኢትዮጵያ በረሃብና ተያያዥ በሽታዎች የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱ የተጠቀሰ ሲሆን፤ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ለእርዳታ የሚልኩት እህል ለግል ጥቅም ሲውል እና በገበያ ላይ ሲሸጥ አረጋግጠናል በሚል የሰብዓዊ እርዳታ መቋረጡም፣ በዚህ ወቅት በረሃብ እና በበሽታ ለሞቱ ሰዎች እንደ ዋና ምክንያት ተጠቅሷል። እንዲሁም በዚያው ዓመት በተፈጠሩ ግጭቶች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ100 ሺሕ በላይ መሆኑን ግሎባል ፒስ ኢንዴክስ በድኅረ ገጹ አስነብቧል፡፡ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት የእርስ በርስ ግጭት…
Read More

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጦርነት 350 ሺህ ሰዎች መገደላቸውን ገለጸች

አሜሪካ ኢትዮጵያን ከሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገርነት ዝርዝር ውስጥ ሰርዛለች። በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ ነበር አሜሪካ ኢትዮጵያን የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጻሚ ሀገር ዝርዝር ውስጥ የመዘገበቻት። ይህን ተከትሎም ዋሽንግተን ለኢትዮጵያ ታደርጋቸው የነበሩ የልማት ስራዎች ድጋፎችን አቋርጣ ቆይታለች። እንደ ፎሬይን ፖሊሲ ዘገባ ከሆነ አሜሪካ ኢትዮጵያ አሁን ላይ የከፋ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጸምባት ሀገር አይደለችም የሚል አቋም ላይ ደርሳለች። በኮሮና ቫይረስ፣ በጦርነት እና በዓለም አቀፍ ንግድ መቀዛቀዝ ምክንያቶች ኢትዮጵያ እንደ ሌሎች ሀገራት የብድር መክፈያ ጊዜ ሽግሽግ እንዲደረግ አስቀድማ ጠይቃ ነበር። ይሁንና አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ በጣለችው እገዳ ምክንያት ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለብዙ በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ያደረጉትን የገንዘብ ድጋፍ ለኢትዮጵያ ማድረግ…
Read More