Admasdigitallottery

ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ የ8 ሚሊዮን ብር ተሸላሚ እድለኛ እንደጠፋበት ገለጸ

ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር በየጊዜው ለሽፓጭ ከሚያውላቸው የእድል ሎተሪዎች መካከል የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አንዱ ነው። 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው ይህ እጣ ባሳለፍነው ጷግሜ 2015 ዓም እጣው የወጣ ሲሆን 1820259 ደግሞ የመጀመሪያ እድለኛ ቁጥር እንደሆነ በወቅቱ ተገልጿል። የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድር ኮሙንኬሽን ዳይሬክተር አቶ ቴድሮስ ንዋይ ለዓልዐይን እንዳሉት "ባሳለፍነው ጷግሜ ላይ ከወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከሶስት እጣ አሸናፊ በስተቀር የሁለት እጣ አሸናፊዎች እስካሁን አልመጡም" ብለዋል። ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳድሩ የሁለት እጣ እድለኞች ማለትም የስምንት ሚሊዮን ብር አሸናፊዎች እስከ ቀጣዩ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ካልመጡ ገንዘቡ ለመንግሥት ገቢ ይሆናልም ብለዋል። 20 ሚሊዮን ብር ከሚያሸልመው እጣ ቁጥር ውስጥ እስካሁን በመተሀራ ከተማ በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ በወዛደርነት…
Read More
የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ ሽልማት ወደ አራት ሚሊዮን አደገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር በቅርቡ የጀመረው አድማስ ድጅታል ሎተሪ የሽልማት መጠኑን ማሳደጉን ገልጿል፡፡ አድማስ ድጅታል ሎተሪ ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ ለአንደኛ አሸናፊ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር በመሸለም ነበር የጀመረው፡፡ በመቀጠልም የሽልማት መጠኑን ወደ ሶስት ሚሊዮን ብር ከፍ የተደረገው አድማስ ድጅታል ሎተሪ ደንበኞች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም በሶስት ብር እና በአምስት ብር የሎተሪ እጣ የሚቆርጡበት የሎተሪ ስርዓት ነው፡፡ በደምበኞች አስተያየት መሰረት ቀደም ሲል የነበበረውን የዕጣ ሽልማት የአንደኛው ዕጣ 4 ሚሊዮን ብር፣ የሁለተኛው ዕጣ 2 ሚሊዮን ብር የሶስተኛው ዕጣ 1 ሚሊዮን ብር በማድረግ ተደርጓል ተብሏል፡፡ እንዲሁም ደንበኞች ከሰኔ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አንድ እጣ በ10 ብር በ605 ላይ ማንኛውም ፊደል በመላክ…
Read More