Blog

በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው እየገቡ መሆኑ ተገለጸ

በሸገር ከተማ አስተዳደር በሚገኘው ኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም ለባለእድለኞች በተላለፉ ቤቶች ውስጥ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ቁልፍ ሰብረው በመግባት ወረራ እየፈጸሙ መሆኑን የኮንዶሚኒየሙ ሕጋዊ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በኮንዶሚኒየሙ የእጣ እድለኞች ሆነው ለባለቤቶች ቁልፍ ተላለፈው፤ ነገር ግን ተቆልፈው በተቀመጡ ቤቶች እና እስካሁን ለባለእድለኞች ባልተላለፉ ቤቶች ላይ የማይታወቁ ሰዎች ወረራ እየፈጸሙ ነው ተብሏል። ይህን ድርጊት ለመከላከል ጥረት በሚያደርጉ የኮንዶሚኒየም የጥበቃ ሠራተኞች ላይም ዛቻ እና ማስፈራሪያ በማድረስ ሰዎቹ በኃይል እየገቡ መሆናቸውን አዲስ ማለዳ ዘግቧል፡፡ ነዋሪዎቹ አክለውም፤ “ተዘግቶ የተቀመጠን ቤት በኃይል ሰብረው ገብተው ወረራ ሲፈጽሙ አንድም የመንግሥት አካል ሊያሰቆማቸው የሞከረ የለም፡፡” ሲሉ ተደምጠዋል። ከመጋቢት 2015 ጀመሮ በኮንዶሚኒየሞቹ ላይ ከፍተኛ ወረራ እየተካሄደ መሆኑን በመጠቆምም፤ “ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል በተደጋጋሚ…
Read More
በኢትዮጵያ ከ15 ሺህ በላይ የካንሰር ህመምተኞች የህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ ከ15 ሺህ በላይ የካንሰር ህመምተኞች የህክምና ወረፋ በመጠባበቅ ላይ መሆናቸው ተገለጸ

የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ፤ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ መኖራቸውን አስታውቋል። የሆስፒታሉ የካንሰር ሕክምና ማዕከል ክፍል ኃላፊ ዶክተር ኤዶም ሰይፉ እንዳሉት "የተለያዩ የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠብቁ ከ2013 መጨረሻ፣ 2014 ዓ.ም. እና 2015 ዓ.ም. ወረፋ ያልደረሳቸው አሉ፡፡ ይሁን እንጂ በየዕለቱ የሚመጡ ድንገተኛ የካንሰር ታካሚዎች በመኖራቸው በቅድሚያ ለእነዚህ ታካሚዎች አገልግሎቱን እንዲያገኙ ይደረጋል። በሆስፒታሉ ቆይተው መታከም ይችላሉ ተብለው የተለዩት ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ ሕክምና ለማግኘት እየተጠባበቁ ያሉትን ለማስተናገድ ጥረት እየተደረገ ነውም ብለዋል። ለዚህ ወረፋ መብዛት ዋነኛ ምክንያት ብለው ያቀረቡት በሆስፒታሉ የሚገኘው መሣሪያ አንድ ብቻ በመሆኑ እንደሆነም ዶክተር ኤዶም ተናግረዋል። በዚህ ዓመት ብቻ በተደረገው ማጣራት የካንሰር ሕክምና ለማግኘት የሚጠበባቁ 5,000…
Read More
በመተከል ዞን በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ

በመተከል ዞን በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ

በመተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ በጉምዝ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 18 ደረሰ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ግልገል በለስ ከተማ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ 18 ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ግድያው የተፈጸመው አርብ ሰኔ 30 ቀን 2015 ሲሆን፤ ከ8 በላይ ሰዎች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ላይ እንደሚገኙም ታውቋል፡፡ እንደነዋሪዎቹ ገለጻ ከሆነ የችግሩ መነሻ፤ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለሥራ በወጣበት ተገድሎ በመገኘቱ አስከሬኑን ለማምጣት በሄዱ የጸጥታ አካላት ላይ በአካባቢው የሚገኙ የጉምዝ ታጣቂዎች ተኩስ በመክፈታቸው ሲሆን፤ በዚህም በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል፡፡ ተኩሱን የከፈቱት ሽፍታ የነበሩ እና የሰላም ተመላሽ ተብለው ትጥቃቸውን ሙሉ ለሙሉ ለመንግሥት እንዲያስረክቡ ከተጠየቁ ታጣቂዎች መካከል ትጥቅ ያልፈቱ እና በጫካ የሚኖሩ ታጣቂዎች…
Read More
ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለ31ኛ ጊዜ አነሳ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የዘንድሮውን የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን አንስቷል። ባህርዳር ከነማ ውድድሩን በሁለተኝነት አጠናቋል። የ2015 የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር በቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ አሸናፊነት ተጠናቋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ64 ነጥብ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ ባህርዳር ከነማ ደግሞ በ60 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን በ49 ነጥቦች የውድድር ዓመቱን አጠናቀዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ክለብ ወይም ፈረሰኞቹ ፕሪምየር ሊጉን ለ31ኛ ጊዜ አሸናፊ ሆነዋል። የወራጅነት ደረጃዎች ላይ ደግሞ አርባምንጭ እግር ኳስ ክለብ በ34 ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ ክለብ በ18 እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ15 ነጥቦች ወደ ከፍተኛ ሊግ ወርደዋል። የኮኮብ ግብ አግቢነት ደረጃውን የቅዱስ ጊዮርጊሱ እስማኤል አጎሮ በ25 የውድድር ዓመቱ ኮኮብ ግብ አግቢ ሆኖ አጠናቋል።
Read More
ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ከ60 ሺሕ በላይ ደረሰ

ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ከ60 ሺሕ በላይ ደረሰ

በሱዳን ብሑራዊ ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ሀይል መካከል ያለውን ግጭት በመሸሽ ከ60 ሺሕ በላይ ሰዎች በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ እና በጋምቤላ ክልሎች በኩል ድንበር አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ገልጿል። በአጠቃላይ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት መካከልም ከ30 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ከ15 ሺሕ በላይ የሚሆኑት ሱዳናውያን ሲሆኑ፤ ከ13 ሺሕ በላይ ያህሉ ደግሞ የሌላ አገር ዜጎች መሆናቸው ተጠቁሟል። የተባበሩት መንግሥታ ድርጅት በአገሪቱ በተቀሰቀሰው ግጭት ከ25 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የገለጸ ሲሆን፤ በአገሪቱ ጾታዊ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱን አስታውቋል። እንዲሁም ጦርነቱ ከተጀመረበት ባለፈው ሚያዚያ ወር አንስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውን፣ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውና ከግማሽ ሚሊዮን…
Read More
ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ቴክኖ ሞባይል ካሞን 20 የተሰኘ ምርቱን ይፋ አደረገ

ዋና መቀመጫውን ቻይና ያደረገው ቴክኖ ሞባይል አዲስ የሞባይል ምርቱን ለኢትዮጵያ ደንበኞቹ በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል። ቴክኖ ሞባይል ይፋ ያደረገው ካሞን 20 አዲስ ምርት የአምስተኛ ትውልድ ወይም 5G ኔትወርክ አገልግሎት መስጠት ያስችላል ተብሏል። እንዲሁም ይህ አዲስ ስልክ 8 ጌጋ ባይት ራም እና 256 ጌጋ ባይት መጠን ያላቸው መረጃዎችን የመያዝ አቅም ሲኖረው ለተክም ሰዓት ማስጠቀም የሚያስችል ባትሪም አለው ተብሏል። ሶስት ካሜራ እንዳለው የተገለጸው ይህ አዲስ የቴክኖ ሞባይል ስልክ ካሳለፍነው ግንቦት ወር ጀምሮ ለደንበኞቹ ቀርቧል። ቴክኖ ሞባይል በትራንሽን ኩባንያ ስር ሆኖ በፈረንጆቹ 2006 ላይ የተመሰረተ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው። በጆርጁ ዙ የተቋቋመው ቴክኖ ሞባይል ዋና መቀመጫውን በቻይናዋ ሸንዘን አድርጎ በመላው ዓለም ምርቶቹን ለደንበኞቹ በማቅረብ…
Read More
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀች

ቤተ ክርስቲያኗ ዘጠኝ ኤጲስ ቆጶሳትን እንደምትሾም አስታውቃለች ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው መግለጫ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ በተፈጸመው ሲመት በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ የደረሰውን መከራና ፈተና ለማሳለፍ ሲባል ዶግማዋን፣ ቀኖናዋን እና ትውፊቷን ባስጠበቀ ሁኔታ ችግሩ በውይይት እንዲፈታ ትረት ስታደርግ መቆየቷን ገልጻለች። በዚህ መሰረትም የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተደረሰው ስምምነት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ግንቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ቀኖናዋን ከስምምነቱ ፤ ስምምነቱን ከቀኖናዋ ጋር በማዛመድ በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልል ባሉ ክፍት አህጉረ ስብከት ተመድበው የሚያገለግሉ 9 ኤጲስ ቆጶሳት በቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲሾሙ…
Read More
ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ ውሀ መያዣ ጊዜን አራዘመች

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስከ መስከረም ውሀ እንደማይዝ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ተናግረዋል። ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ እየሰጡ ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ከአባላቱ ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚንስትሩ በዚህ ጊዜ እንዳሉት የኢትዮጵያ ህዳሴው ግድብ ውሀ ሙሌት አይከናወንም ብለዋል። "ኢትዮጵያ የሱዳንን እና ግብፅ ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የህዳሴ ግድብ ሙሌቱ እስከ መስከረም መጀመሪያ አታከናውንም" ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ ተናግረዋል። ታላቁ የህዳሴ ግድብ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሀምሌ ወር ጀምር ውሀ ሲይዝ የቆየ ሲሆን ዘንድሮ ግን ውሀ የመያዣው ጊዜ ወደ መስከረም መዛወሩ ተገልጿል። እንደ ጠቅላይ ሚንስትሩ ገለጻ የዘንድሮው ውሀ ሙሌት ወደ ግብጽ እና ሱዳን በቂ የዉሃ ከደረሰ በኋላ ሙሌቱ…
Read More
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄዎች በመቀበል ላይ ናቸው። የባህርዳር ህዝብን ወክለው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ጥያቄ አቅርበዋል።የአብን ተወካዩ እንዳሉት "ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደስልጣን ከመጡ ወዲህ ኢኮኖሚዉ ታሟል፣ ወጣቶች ሀገራቸዉ ዉስጥ ተስፋ በማጣታቸው ስደትን ምርጫቸዉ አድርገዋል" ብለዋል። "ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ይታገታሉ ፣ ብልጽግና መራሹ ፓርቲ ሀገሪቱ ከገባችበት ቅርቃር ማዉጣት አልቻለም" ያሉት የምክር ቤቱ አባሉ ስልጣኖን ለጊዜያዊ አስተዳደር እንዲያስረክቡ ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩን ጠይቀዋል። ሌላኛው የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አዳነ ተሾመ በበኩላቸው " ዜጎችን በማገት በሚሊዮን ገንዘብ መጠየቅ የዜጎችን ሰላም ወጥቶ መግባት ጥያቄ ዉስጥ ከትቶታል። በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ…
Read More
አባቱን በቤንዚል አቃጥሎ የገደለው ሰው በፖሊስ ተያዘ

አባቱን በቤንዚል አቃጥሎ የገደለው ሰው በፖሊስ ተያዘ

ፖሊስ በአዲስ አበባ ወላጅ አባቱን በቤንዚን አቃጥሎ የገደለን ተጠጣሪ መያዙን ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ ቤተሰቦቼ ለእኔ ምንም ቦታ የላቸውም በሚል ምክንያት ወላጅ አባቱንና ታላቅ ወንድሙን ቤንዚል በመርጨት በቁም ያቃጠላቸው ተከሳሽ በቁጥጥር ማዋሉን ገልጿል። ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመው በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ክብረ ደመና ሙሉ ወንጌል አካባቢ ሰኔ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ነው ተብሏል። ተከሳሹ ከዚህ ቀደም በሌላ ወንጀል ተከሶ ታስሮ የነበረና በፍርድ ቤት ዋስትና የተለቀቀ እንደነበር የገለጸው ፖሊስ ከእናቴ በስተቀር ለእኔ የሚያስብልኝ የለም በሚል ምክንያት ወንጀሉን ለመፈጸም እንደተነሳሳም ተገልጿል። ከሳምንት በፊትም በአንድ ሺህ ስድስት መቶ ብር ቤንዚል በመግዛት አባቱና ታላቅ…
Read More