Blog

ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ቦይንግ ኩባንያ ከቲንክ ያንግ ጋር በመተባበር ለ60 ኢትዮጵያዊያን ስልጠና ሰጠ

ለአራት ቀናት የተሰጠው ይህ ስልጠና ከቲንክ ያንግ እና ከአሜሪካው የአቪዬሽን ቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር ነው። ስልጠናው ከ20 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ለ60 ተማሪዎች በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። ከሰባት ዓመት በላይ ጀምሮ እድሜ ላላቸው የተሰጠው ይህ ስልጠና ታዳጊዎች ከቴክኖሎጂ ጋር እየተዋወቁ እንዲያድጉ በማሰብ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል። ለታዳጊዎቹ የተሰጠው የስልጠና አይነት ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ሮቦቲንግ፣ ኮዲንግ እና አርቲፊሻል እንተለጀንስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ የስልጠናው አካል ሲሆን የበጀት ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል። በቦይንግ ኩባንያ የመካከለኛው ምስራቅ፣ አፍሪካ እና ተርኪየ ፕሬዝዳንት የሆኑት ኩልጅት ጋታ ስልጠናው የቦይንግ ማህበራዊ ሀላፊነት አንዱ አካል ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ መንግሥት ድጅታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘውን እቅድ ለመደገፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥተናል ያሉት"…
Read More
ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

ኢትዮጵያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የጣለችውን ገደብ አነሳች

በኢትዮጽያ ለወራት ያህል በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ ተነስቷል። በኢትዮጵያ ከየካቲት ወር መጀመሪያ አንስቶ በኢንተርኔት አገልግሎቶች ማለትም በፌስቡክ፣ ሜሴንጀር፣ ቴሌግራም እና ቲክቶክ ላይ ገደብ መጣሉ ይታወሳል። በኢትዮጵያ የኢንተርኔት ገደብ መጣሉን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች መንግሥት ገደቡን እንዲያነሳ ሲጠየቅ ቆይቷል። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት…
Read More
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለማችን ቀዳሚ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ

የአልናስር አጥቂ የሆነው ፖርቹጋላዊው ክርስቲያኖ ሮናልድ የ2023 ከፍተኛ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆኖ ተመዝግቧል። እንደ ፎርብስ ዘገባ ከሆነ የአምስት ጊዜ ባሎንዶር ተሸላሚው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በተያዘው ዓመት ብቻ 136 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል። የዓለም ዋንጫ አሸናፊው አርጀንቲናዊው ሊዮኔል ሜሲ በ2022 ዓመት 130 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ተከፍሎታል። ክርስቲያኖ ካገኘው የ136 ሚሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ውስጥ 90 ሚሊዮን ዶላሩን ከሜዳ ውጪ ማለትም ከማስታወቂያ እና ስፖንሰር ስራዎች ማግኘቱ ተገልጿል። በማንችስተር ዩናይትድን ባለ መግባባት ወደ ሳውዲ አረቢያው አልናስር ያመራው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ደመወዙ እጥፍ እንዳደገለትም ተገልጿል። በአጠቃላይ በስፖርቱ ዘርፍ ሊዮኔል ሜሲ እና ክሊያን ምባፔ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ በመቀጠል ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዱረጃን ይዘዋል። የቅርጫት ኳስ ኮኮቡ ለቦርን 119 ሚሊዮን…
Read More
አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

አርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት እንዲሰጣት ተወሰነ

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለአርቲስት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ሊሰጣት መወሰኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ሐምሌ 13/2015 እንደሚያስመርቅ የገለጹት ፕሬዘዳንቱ፤ በዕለቱ ለተወዳጇ አርቲስት እጅጋየው ሽባባው(ጂጂ) የክብር ዶክትሬት ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል። ድምፃዊት፣ ገጣሚ፣ የዜማ ደራሲ እና ተዋናይት የሆነችው ሁለገቧ አርቲስት ጂጂ፣ የአገሯን ባህልና ሙዚቃ ለዓለም በማስተዋወቅ እንዲሁም በኪነጥበብ የአዊን ህዝብ ቋንቋ እና ባህል በማሳደግ ላበረከተችው አስተዋፅኦ የክብር ዶክትሬቱ እንደሚበረከትላት ነው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት መግለጻቸውን ከዩንቨርስቲው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። ለጂጂ የሚሰጠውን የክብር ዶክትሬት እና የተማሪዎቹን የምርቃት ሥነስርዓት በማስመልከት ረቡዕ ማለትም ሐምሌ 12/2015 ከቀኑ 8:00 ሰዓት ለመገናኛ ብዙሀን ዝርዝር መግለጫ እንደሚሰጥም ፕሬዘዳንቱ ገልጸዋል። ከሰሞኑ ለ15ተኛ ጊዜ በተካሄደዉ የአማራ…
Read More
ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኢትዮጵያ በሰኔ ወር መጨረሻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያንን አፈናቀላለች ሲል ገልጿል፡፡ ተመድ ኢትዮጵያ  የኤርትራ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን፤ የስደተኞችን ሕግን በመጣስ እንዲሁም ክስ ሳይኖርባቸው በዘፈቀደ የማሰር እና የማፈናቀል ተግባሯን በአስቸኳይ እንደታቆም ነው ያሳሰበው። ድርጅቱ ወደ ሌላ አገር ጥገኝነት ጠይቀው የገቡ ስደተኞችን በጅምላ ማባረርና በዘፈቀደ ማሰር በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ ነው ሲልም ገልጿል፡፡ በዚህም የመንግሥታቱ ድርጅት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን ጥገኝነት ጠያቂዎችን የማሰቃየት፤ በግዳጅ የማፈናቅልና የሰብአዊ መብት ረገጣ አውግዟል። ኢትዮጵያ በሱዳን ጥገኝነት ጠይቀው ሲኖሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ወደ አገሪቷ የገቡ ኤርትራውያን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ አያያዝ እየተፈጸመች ነው የተባለ ሲሆን፤ ይህም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶችን ሙሉ ለሙሉ የጣሰ ድርጊት…
Read More
ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ኢንተርኔት በመዝጋቷ ምክንያት ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማጣቷ ተገለጸ

ኢትዮጵያ ከያዝነው ዓመት የካቲት ወር ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ባሉት አምስት ወራት በኢንተርኔት አገልግሎት ላይ ገደብ ጥላለች። ኢትዮጵያ የኢንተርኔት እገዳውን የጣለችው በቲክቶክ፣ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ እና ዩቲዩብ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ነው። በኢንተርኔት እገዳው ምክንያትም ኢትዮጵያ 7 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማጣቷን የመብቶችና ዴሞክራሲ እድገት ማዕከል ገልጿል፡፡ “ፖለቲካዊ አለመረጋጋቶችን ተከትሎ፤ ከ2008 ወዲህ የበይነመረብ ግንኙነትን ማቋረጥ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣ ችግር ነው” ያለው ማዕከሉ፤ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጡ የዴሞክራሲና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዕድገት ጸር መሆኑን አመላክቷል፡፡ መንግሥት ዋና ዋና የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በኢትዮጵያ እንዳይጎበኙ እገዳ መጣሉ ሕጋዊ መሰረት የሌለው ነው ሲልም ገልጿል፡፡ የበይነመረብ ግንኙነት መቋረጥ ትኩረት ሊያገኝ ባለመቻሉም የሰብዓዊ መብቶች እሴቶችን እንዲሁም በሕገ መንግሥቱ የተጠበቁ…
Read More
በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በአዲስ አበባ የባለ ትዳሮች ፍቺ በ60 በመቶ ጨመረ

በከተማዋ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ከ4 ሺህ በላይ ትዳር መፍረሱ ተገልጿል የፈረሰው ትዳር ቁጥር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር በ60 በመቶ ጨምሯል ተብሏል በተጠናቀቀው የ2015 በጀት ዓመት 4 ሺህ 696 ትዳር በፍቺ መጠናቀቁ ተገልጿል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዮሴፍ ንጉሴ እንደገለፁት በ2015 ዓ.ም ከማዕከል እስከ ወረዳ ለ2 ሚሊየን 239 ሺህ 713 ተገልጋዮች አገልግሎት ተሰጥቷል። ከዚህ ውስጥ 37 ሺህ 397 ጋብቻ እና 4 ሺህ 696 ፍቺ መሆኑን ተናግረዋል። ዘንድሮ የተመዘገበው የፍቺ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር፥ የ60 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል። ለአብነትም በ2014 ዓ.ም 2 ሺህ 937 ፍቺ መመዝገቡን እና በ2015 ዓ.ም ወደ…
Read More
ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ኢትዮጵያ እና ግብጽ በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ በአራት ወራት ውስጥ ችግራቸውን ለመፍታት ተስማሙ

ግብጽ በሱዳን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ያለመ ውይይት የጎረቤት ሀገራት መሪዎችን መጋበዟ ይታወሳል። ኢትዮጵያን ጨምሮ የሱዳን ጎረቤት ሀገራት በመድረኩ ላይ ለመሳተፍ ወደ ካይሮ ያመሩ ሲሆን ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከውይይቱ በተጓዳኝ ከፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ጋር መወያየታቸው ተገልጿል። የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ መወያየታቸው ሲገለጽ የግድቡ ውሀ አሞላል ደግሞ የመሪዎቹ ዋነኛ መወያያ እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ መሰረትም ኢትዮጵያ በግድቡ ውሀ አሞላል ዙሪያ ግብጽን እና ሱዳንን የመጉዳት ፍላጎት የላትም የተባለ ሲሆን በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ ስለመስማማታቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳንም በህዳሴው ግድብ ውሀ አሞላል እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያለባቸውን አለመግባባት በአራት ወራት ውስጥ በሚያደርጉት ውይይት ወደ…
Read More
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዳይሬክተር ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዳይሬክተር ከሀላፊነታቸው ለቀቁ

የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጂማ ዲልቦ በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸውን አስታውቀዋል። ዳይሬክተሩ ከአራት ዓመታ በላይ ከመሩት ተቋም ስራቸውን ለመልቀቅ ያቀረቡት ጥያቄ በመንግስት ተቀባይነት ማግኘቱን ተናግረዋል፡፡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ኃላፊ ስራቸውን ለምን እንደለቀቁ ያሉት ነገር የለም። ጂማ ዲልቦ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ "ዘርፉ ከነበረበት ድባቴ ወጥቶ ለሀገር ልማትና ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አስተዋጽኦ ማበርከት መጀመሩ በቀጣይ ዓመታት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋ አደርጋለሁ" ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በጦርነት ምክንያት የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ቁጥር እያደገ የመጣ ቢሆንም በዛው ልክ ግን ሰራተኞቻቸው እየተገደሉባቸው መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል። ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ36 በላይ ለተቸገሩ ዜጎች ድጋፍ ለማድረስ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ እንደተገደሉ ተገልጿል።…
Read More
ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

ኢትዮጵያ ለታራሚዎች የመንጃ ፈቃድ ስልጠና መስጠት ጀመረች

በኢትዮጲያ ለመጀመሪያ ጊዜ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት የመንጃ ፍቃድ ስልጠና መስጠት ተጀመረ አሁን ላይ 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል ተብሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር ጀኔራል ዳመና ዳሮታ እንዳሉት ለመጀመሪያ ጊዜ በዝዋይ ማረሚያ ማዕከል ለታራሚዎች የአሽከርካሪ መንጃ ፍቃድ ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል፡፡ ስልጠናው በማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ታሪክ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል የመጀመሪያው ሲሆን ታራሚዎች የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ በቀጥታ ወደ ስራ አለም እንዲገቡ የሚያግዝ ነው ተብሏል። ለመጀመሪያ ጊዜ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ማእከል ሲከፍት ለታራሚው እና ለፖሊስ አባላት እንዲያገለግል ታስቦ ሲሆን እስካሁን 22 ታራሚዎች ስልጠናውን እየወሰዱ ይገኛል። የህግ ታራሚዎችን በይበልጥ የሙያ ባለቤት የማድረግ ስራ በቀጣይ በማስፋፋት ከመንጃ ፍቃድ በተጨማሪ የመካኒክነት ስልጠናና የተሽከርካሪ…
Read More