Refugees

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያን ስደተኞች እየተዋከቡ ነው መባሉን አስተባበለች

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያን ስደተኞች እየተዋከቡ ነው መባሉን አስተባበለች

በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞች በመንግሥት እየተዋከቡ ነው መባሉን የስደተኞችና ተመላሾች አግልግሎት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል፡፡አገልግሎቱ በመግለጫው በኢትዮጵያ የተጠለሉ ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም ብሏል፡፡ ከሰሞኑ እንደ በርካታ አለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጨምሮ በስፋት የተዘገበው የኤርትራዊያን በአዲስ አበባ መዋከብ ከእውነታው የራቀ ነው በማት አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡ በኢትዮጵያ በተለይም በአዲስ አበባ በሚገኙ በኤርትራውያን ላይ የጅምላ እስራት እየተፈጸመባቸው መሆኑ ከሰሞኑ ሲዘገብ ነበር፡፡ ምንም እንኳን መሰል ክስተቶች አዲስ ባይሆኑም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው መጠነ ሰፊ የጅምላ እስራት ግን ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረባቸው ኤርትራውያን ከሰሞኑ ለቪኦኤ መናገራቸው ይታወሳል።ይሁን እንጂ የስደተኞችን ጉዳይ የሚከታተለው አገልግቱ በሰጠው ምላሽ በኢትዮጵያ የሚገኙ…
Read More
ኢትዮጵያ ስደተኞች ስራ እንዲቀጠሩ እና እንዲነግዱ ፈቀደች፡፡

ኢትዮጵያ ስደተኞች ስራ እንዲቀጠሩ እና እንዲነግዱ ፈቀደች፡፡

አንድ ሚሊዮን ገደማ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ያስጠለለችው ኢትዮጵያ እውቅና ያገኙ ስደተኞች ስራ መቀጠር የሚያስችላቸውን መመሪያ ማዘጋጀቷን አስታውቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት እንዳስታወቀው በ2011 ዓ/ም ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ስደተኞች እና ጥገኝነት ጠያቂዎች ስራ መቀጠርን ጨምሮ ሌሎች ጥቅሞችን እንዲያገኙ የሚያደርገው ህግ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁን አስታውቋል፡፡ ይህ አዋጅ የተደነገገውን ዕውቅና ያገኙ ስደተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን እንዲሁም የተቀባይ ማህበረሰቦችን የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚል የተዘጋጀ ነውም ተብሏል፡፡ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎትም የስደተኞችን የመስራት መብት ለማስፈፀም “ስደተኞች በስራ ላይ የሚሰማሩበትን ሁኔታ ለመወሰን መመሪያ አዘጋጅቶ እንደነበር አስታውቋል፡፡ መመሪያ ቁጥር 02/2012 በሚል የተዘጋጀው ይህ ሰነድም የስደተኞች ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1110/2010 የያዛቸውን መብቶች…
Read More
ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው ተገለጸ

ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት መሰደዳቸው ተገለጸ

ባለፉት አምስት ዓመታት ከ800 ሺህ በላይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ውጭ ሀገራት ፈልሰዋል የተባለ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 78 በመቶ የሚሆኑት ወጣት ከመሆናቸውም በላይ አብዛኞቹ ሴቶች መሆናቸው ተነግሯል ። የኢትዮጵያ ዜጎች በስራ ዕድል እጦት የተነሣ በተለያዩ መተላለፊያዎች ድንበር አቋርጠው እንደሚፈልሱ የተገለፀ ሲሆን ድህነት ፣ የሰላም እጦት፣ የመነሻ ሐብት ምንጭ እጥረት ፣ የአየር ንብረት መለዋወጥና የተፈጥሮ ውድመት ዋና ዋና ገፊ ምክንያቶች እንደሆኑ ተገልጿል ። በሌላ በኩል ኢትዮጵያዊያን ድንበር አቋርጠው እንዲፈልሱ ሳቢ ከሆኑ ምክንያቶች መካከል ለራሳቸውና ቤተሰባቸው ገቢ የማመንጨት  ፍላጎት መኖር እና  የተሻለ ህይወት ፍለጋ እንደሆነ ይጠቀሳሉ ተብሏል ። የኢትዮጵያ ፍልሰተኛ ሰራተኞች ለኢትዮጵያ መልካም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ሲሆን ሀገሪቱ ውጭ ከሚኖሩና ከሚሰሩ ዜጎቿ ዳጎስ…
Read More
ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ከማፈናቀል እንድትታቀብ ተመድ ጠየቀ

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኢትዮጵያ በሰኔ ወር መጨረሻ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኤርትራውያንን አፈናቀላለች ሲል ገልጿል፡፡ ተመድ ኢትዮጵያ  የኤርትራ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን፤ የስደተኞችን ሕግን በመጣስ እንዲሁም ክስ ሳይኖርባቸው በዘፈቀደ የማሰር እና የማፈናቀል ተግባሯን በአስቸኳይ እንደታቆም ነው ያሳሰበው። ድርጅቱ ወደ ሌላ አገር ጥገኝነት ጠይቀው የገቡ ስደተኞችን በጅምላ ማባረርና በዘፈቀደ ማሰር በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ ነው ሲልም ገልጿል፡፡ በዚህም የመንግሥታቱ ድርጅት ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን ጥገኝነት ጠያቂዎችን የማሰቃየት፤ በግዳጅ የማፈናቅልና የሰብአዊ መብት ረገጣ አውግዟል። ኢትዮጵያ በሱዳን ጥገኝነት ጠይቀው ሲኖሩ የነበሩና በጦርነቱ ምክንያት ወደ አገሪቷ የገቡ ኤርትራውያን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ኢ-ሰብአዊ አያያዝ እየተፈጸመች ነው የተባለ ሲሆን፤ ይህም ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ስምምነቶችን ሙሉ ለሙሉ የጣሰ ድርጊት…
Read More