17
Jul
ለአራት ቀናት የተሰጠው ይህ ስልጠና ከቲንክ ያንግ እና ከአሜሪካው የአቪዬሽን ቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር ነው። ስልጠናው ከ20 ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ለ60 ተማሪዎች በአዲስ አበባ ተሰጥቷል። ከሰባት ዓመት በላይ ጀምሮ እድሜ ላላቸው የተሰጠው ይህ ስልጠና ታዳጊዎች ከቴክኖሎጂ ጋር እየተዋወቁ እንዲያድጉ በማሰብ የተዘጋጀ እንደሆነ ተገልጿል። ለታዳጊዎቹ የተሰጠው የስልጠና አይነት ዌብሳይት ማበልጸግ፣ ሮቦቲንግ፣ ኮዲንግ እና አርቲፊሻል እንተለጀንስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። ዓለም አቀፉ የአቪዬሽን ተቋም ቦይንግ የስልጠናው አካል ሲሆን የበጀት ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል። በቦይንግ ኩባንያ የመካከለኛው ምስራቅ፣ አፍሪካ እና ተርኪየ ፕሬዝዳንት የሆኑት ኩልጅት ጋታ ስልጠናው የቦይንግ ማህበራዊ ሀላፊነት አንዱ አካል ነው ብለዋል። "የኢትዮጵያ መንግሥት ድጅታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የያዘውን እቅድ ለመደገፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥተናል ያሉት"…