Dessalegnchane

ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና አብዲ ኢሌ ከእስር ተፈቱ

ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ጀነራል ክንፈ ዳኘው እና አብዲ ኢሌ ከእስር ተፈቱ

በ2013 በተካሄደው ስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በባህርዳር ከተማ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ተወዳድረው የተመረጡት እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ታስረው ነበር፡፡ ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በመታወቂያ ዋስትና ከእስር ተለቀዋል። የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ከሁለት ወራት በፊት በጸጥታ ሀይሎች ተይዘው የታሰሩ ቢሆንም ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቆይተው ዛሬ ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸውን ጠበቃቸው ተናግረዋል። ባሳለፍነው ሀምሌ ወር ላይ በተመሳሳይ ከመኖሪያ ቤታቸው በጸጽታ ሀይሎች ተወስደው በእስር ላይ የነበሩት ሌላኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ያለመከሰስ መብታቸው ከታሰሩ ከሰባት…
Read More
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣን እንዲለቁ ተጠየቁ

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄዎች በመቀበል ላይ ናቸው። የባህርዳር ህዝብን ወክለው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያሉት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ጥያቄ አቅርበዋል።የአብን ተወካዩ እንዳሉት "ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደስልጣን ከመጡ ወዲህ ኢኮኖሚዉ ታሟል፣ ወጣቶች ሀገራቸዉ ዉስጥ ተስፋ በማጣታቸው ስደትን ምርጫቸዉ አድርገዋል" ብለዋል። "ዜጎች በጠራራ ፀሀይ ይታገታሉ ፣ ብልጽግና መራሹ ፓርቲ ሀገሪቱ ከገባችበት ቅርቃር ማዉጣት አልቻለም" ያሉት የምክር ቤቱ አባሉ ስልጣኖን ለጊዜያዊ አስተዳደር እንዲያስረክቡ ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩን ጠይቀዋል። ሌላኛው የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ አዳነ ተሾመ በበኩላቸው " ዜጎችን በማገት በሚሊዮን ገንዘብ መጠየቅ የዜጎችን ሰላም ወጥቶ መግባት ጥያቄ ዉስጥ ከትቶታል። በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ…
Read More