30
Jun
በፓስተር ዮናታን ንብረቶች ላይ ንብ ባንክ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ አወጣ። ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ ላበደረው ንብረት የሐራጅ ሽያጭ አውጥቷል። ንብ ባንክ በሰኔ 22 ቀን የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ባስወጣው የሀራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ መሰረት በአዲስ አበባ እና ሀዋሳ ባሉ የመኖሪያ ቤት እና ንግድ ድርጅቶችን ለመሸጥ ለተጫራጮች ማስታወቂያ አውጥቷል። አበዳሪው ወይም የመያዢያ ሰጪ ስም፣ አበዳሪው ቅርንጫፍ፣ የሚሸጠው ንብረት ዓይነትና የሚገኝበት ቦታ፣ የሐራጁ መነሻ በብር፣ የሐራጁ ቀንና ሰዓትም ተገልጿል። ጨረታ ከወጣባቸው ንብረቶች መካለም አቶ ዮናታን አኪሊሉ አንጀሎ አራት ኪሎ ፕሪሚየም፣ በስማቸው የተመዘገበ ሀዋሳ ምሥራቅ ከተማ የሚገኝ 400 ሜትር ካሬ ቦታ ያለው ባለ 3 ወለል መኖሪያ ቤት ሲሆን የሐራጁ መነሻ ዋጋ 22 ሚሊዮን ብር…