Blog

ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ለ15ኛ ጊዜ ሎተሪ የደረሳቸው የጎንደሩ እድለኛ አባት

ግለሰቡ በአንድ ዓመት ውስጥ የገናን እና ፋሲካ በዓል ሎተሪን አሸንፈዋል አቶ መሃመድ አህመድ አህመድ ይባላሉ፤ተወልደው ያደጉት ጎንደር ነው፡፡ አቶ መሃመድ ሙሉ ስማቸው መሃመድ አህመድ ቢሆንም በተደጋጋሚ ሎተሪ ስለጎበኛቸው የአባታቸው ስም ወደ ሎተሪ ተቀይሮ በሚኖሩበት ከተማ መሃመድ ሎተሪ እየተባሉ በመጠራት ላይ ናቸው፡፡ አቶ መሃመድ ሎተሪ 15 ጊዜ የሎተሪ እድል አሸናፊ መሆናቸውን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር መረጃ ያመላከታል፡፡ ከ1977 አመት ጀምሮ እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ሎተሪ ቆርጠው ያጡት ብር እንደሌለ እኝህ አባት ይናገራሉ፡፡ አቶ መሃመድ ከ500 ብር ጀምሮ እስከ 75ሺህ ብር ድረስ አሸናፊ ሆነዋል፡፡ የእኝህ አባት እድለኝነት የሚያስገርመው ደግሞ የገና ሎተሪ እጣ አሸናፊ ሆነው በዛው አመት በፋሲካም አሸናፊ መሆናቸው ነው፡፡ በሎተሪ ተስፋ ቆርጠው…
Read More
ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ አቀረበች

ኢትዮጵያ ብሪክስን ለመቀላቀል ጥያቄ አቀረበች

የኢትዮጵያ መንግስት በፈረንጆቹ 2009 የተመሰተረተውንና ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ በጥምረት የመሰረቱትን "ብሪክስ" (BRICS) የተሰኘ የአገራት ስብስብ ለመቀላቀል ጥያቄ ማቅረቧን አስታውቃለች፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም በሳምንታዊ መግለጫቸው እንደገለጹት ኢትዮጵያ የብዙ አለማቀፍ ተቋም መስራች መሆኗን ጠቅሰው የተባበሩት መንግስታት፣ የአፍሪካ ህብረት እና የገለልተኛ አገሮች ንቅናቄና መስራችና ጠንካራ ተሳትፎ ያላት አገር ናት ብለዋል፡፡ በመሆኑም አሁን እየተለወጠ ባለው የዓለም ሁኔታና የኃይል አሰላላፍ አንጻር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን ለማረጋገጥ የሚረዱ ዓለም አቀፍ ተቋማት አባል በመሆን መንግሥት እንደሚሠራ ተናግረዋል። "ከእነዚህ ተቋማት መካከል አንዱ 'ብሪክስ' ነው ፣ ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ጥያቄ ቀርቧል፣ በጎ ምላሻ ያገኛል ብለን እናስባለን ፣ ክትትልም የምናደርግበትም ይሆናል" ብለዋል…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአንዋር ሶሳ ምትክ አዲስ ሀላፊ ሾመ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አዲስ ሀላፊ ተሾመለት። ላለፉት ሁለት ዓመታት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያን በሀላፊነት ሲመሩ የቆዩት አንዋር ሶሳ መልቀቃቸው ይታወሳል። ድርጅቱ ባሳለፍነው ሳምንት እንዳለው አንዋር ሶሳ ከቀጣዩ ወር ጀምሮ በሀላፊነታቸው እንደማይቀጥሉ አስታውቋል። ይህን ተከትሎም የቀድሞው የኤምቲኤን ኡጋንዳ ሀላፊ የነበሩት ዊም ቫንሄልፑት አንዋር ሶሳን ተክተው ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ሮይተርስ ዘግቧል። በዜግነት ቤልጂየማዊ የሆኑት አዲስ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ስራ አስፈጻሚ ከቀጣዩ መስከረም ጀምሮ ድርጅቱን መምራት ይጀምራሉ። ሳፋሪሎም ኢትዮጵያ በኤምፔሳ አማካኝነት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ፈቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። በፈረንሳይ የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የሆኑት ሔኖክ ተፈራን የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሶስት ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራቱንም አስታውቋል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከኢትዮ ቴሌሎም ብርቱ…
Read More
ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ኢትዮጵያ የቀድሞ የባህር ሀይል የውጊያ ጀልባዎችን ለግዳጅ ዝግጁ አደረገች

ወደብ አልባ የሆነችው የኢትዮጵያ መከላከያ ዋና አዘዥ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን ጎብኝተዋል፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ወደ አገልግሎት የመለሳቸውን ፈጣን ተዋጊ ጀልባዎችን እንደጎበኙ የሀገር መካለከያ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ተዋጊ ጀልባዎቹ በቀድሞ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አገልግሎት የሠጡ ሲሆን ዳግም የባሕር ኃይሉን ዝግጁነት ያጠናክራሉም ተብሏል። የአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል ከ30 አመት በላይ ተገለው እና አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ጀልባዎችን የፈጣን ተዋጊ ጀልባ ቴክኖሎጂ እና መሳሪያዎች በመግጠም ለግዳጅ ዝግጁ መደረጋቸውም ተገልጿል። ኢትዮጵያ የባህር ሀይልን እንዳዲስ በማደራጀት ላይ መሆኗን ከሁለት ዓመት በፊት መግለጿ ይታወሳል፡፡ የቀድሞ የኢትዮጵያ አካል የሆነችው ኤርትራ…
Read More
ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ የነበረ ሩሲያዊ ዜጋ ህይወቱ አለፈ

ግለሰቡ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማን በመጎብኘት ላይ እያለ ህይወቱ ማለፉ ተገልጿል፡፡ የ55 ዓመት እድሜ እንዳለው የተገለጸው ይህ ሩሲያዊ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ ሀይቅ ላይ በመዋኘት ላይ እያሉ ህይወቱ አልፏል ተብሏል፡፡ በቢሾፍቱ ኩርፊቱ ሀይቅ በመዝናናት ላይ ከነበሩት የዉጭ ሀገር ዜጎች መካከል አንድ የሩሲያ ዜግነት ያለዉ የ 55 ዓመት ህይወቱ ማለፉን እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደተናገሩት ግለሰቡን ለሞት ያበቃዉ በኩሪፍቱ ሀይቅ 150 ሜትር ጥልቀት ባለው ኩሪፍቱ ሀይቅ ዘልቆ በመዋኘት ላይ ሳለ ህይወቱ ማለፉን ተገልጿል፡፡ ግለሰቡ ባሳለፍነው እሁድ ሰኔ 18 ቀን 2015 ዓ.ም ለመዋኘት ወደ ሀይቁ ውስጠኛው ክፍል ከገባ በኋላ ሳይመለስ ቀርቷል…
Read More
ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ

ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሀላፊነት ለቀቁ ከ2011 ዓ.ም ታህሳስ ወር ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሆነው ስራ የጀመሩት ወይዘሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ በጠየና ምክንያት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ሰማያዊ ማረጋገጫ ባለው የፌስቡክ ገጻቸው ላይ ገልጸዋል፡፡ “ባለፉት  አራት አመት ከስድስት ወራት ሶስት ህዝበ ውሳኔዎችን እና አገራዊ ምርጫን በማካሄድ እና ፓለቲካ ፓርቲዎችን በማስተዳደር የተሰጡኝን ሃላፊነቶች ህጋዊነት ፍትሀዊነት እና ቅንነትን በተከተለ ሁኔታ ለማከናወን ስጥር ቆይቻለሁ” ብለዋል። “ሆኖም ጤናዬን በሚገባ ለመጠበቅ የረጅም ጊዜ እረፍት የሚያስፈልገኝ ሆኖ በመገኘቱ ከ ነሀሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቦርድ ሰብሳቢነቴ በገዛ ፍቃዴ  መልቀቄን ለተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ጽህፈት ቤት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም አሳውቄያለሁ” ሲሉም…
Read More
ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች

ኢትዮጵያ ከ60 ሺህ ቶን በላይ እቃ የመጫን አቅም ያላትን መርከብ ተረከበች የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ በቅርቡ ባህር ዳር እና ሀዋሳ የተሰኙ ሁለት መርከቦች ለኪሳራ ዳርገውኛል በሚል መሸጡ ይታወሳል። በተሸጡት ሁለት መርከቦች ምትክም አባይ የተሰኘች አዲስ መርከብ ከቻይና መግዛቱን አስታውቋል። አዲሷ መርከብም በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት ታሪክ በግዙፍነቷ አቻ የላትም የተባለ ሲሆን መርከቧ በኢትዮጵያ እጅ መግባቷን ድርጅቱ አስታውቋል። የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ድርጅት በ3 ሺህ ቶን የመጫን አቅም ባላቸው መርከቦች ስራውን መጀመሩ ይታወሳል። ኢትዮጵያ የተረከበቻት አባይ የተሰኘችው አዲሷ መርከብ 63 ሺህ 229 ቶን የመጫን አቅም አላት ተብሏል። በቻይናው ያንግዡ ዳያንግ ሺፕ ቢዩልዲንግ የተገነባችው ይህች መርከብ 200 ሜትር ርዝመት እንዳላትም ተገልጿል። ይሁንና…
Read More
ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

ተጠባቂው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቡና ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ

28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ጨዋታ የሊጉ መሪ የሆነው ቅዱስ ጊዮርጊስን ከኢትዮጵያ ቡና አገናኝቷል። በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል። እስማኤል ኦሮ አጎሮ ቅዱስ ጊዮርጊስን ቀዳሚ ያደረገች ጎል ሲያስቆጥር ብሩክ በየነ ደግሞ የኢትዮጵያ ቡናን አቻ ያደረገች ጎል አስቆጥሯል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ የሊጉ መርሐግብር ከመቻል ጋር እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር የሚጫወቱ ይሆናል ተብሏል። ከአራት ቀናት በኋላም ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና፣ አርባምንጭ ከተማ ከድሬዳዋ፣ ወላይታ ዲቻ ከወልቂጤ ከተማ፣ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ መድህን እንዲሁም ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከፋሲል ከነማ ይጫወታሉ። ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊጉን በ59 ነጥቦች ሲመራ ባህርዳር በ54 እንዲሁም ኢትዮጵያ መድን ደግሞ በ48 ነጥብ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃን ይዘዋል።…
Read More
በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በኢትዮጵያ በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ

በአንድ ዓመት ውስጥ ደግሞ ከ5 ሺህ በላይ ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰላም ጥናት ማዕከል አስታውቋል የኢትዮጵያ ፒስ ኢብዘርቫቶሪ የተሰኘው ተቋም ባወጣው ሪፖርት መሰረት በአንድ ሳምንት ውስጥ 100 ኢትዮጵያዊያን ተገድለዋል ብሏል። ከሰኔ 3 ቀን እስከ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በተፈጠሩ የፖለቲካ ግጭቶች ምክንያት 100 ሰዎች መገደላቸውን የግጭት ሁኔታ መረጃዎችን የሚያቀርበው “ኢትዮጵያ ፒስ ኦብዘርቫቶሪ” አስታውቋል። ዓለም አቀፍ የግጭት ሁኔታ እና የክስተት የመረጃ በመሰብሰብና በመተንተን የሚታወቀው “The Armed Conflict Location & Event Data Project” የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ይህንኑ ሥራ በኢትዮጵያ እንዲሠራ በፕሮጀክት ደረጃ ያቋቋመው፣ “Ethiopia Peace Observatory” የተባለው ተቋም ባወጣው ሳምታዊ ሪፖርት፤ በሳምንቱ ከተገደሉት 100…
Read More
ኢትዮ ቴሌኮም 52 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

ኢትዮ ቴሌኮም 52 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ገለጸ

ድርጅቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 103 ሚሊዮን ዶላር ማስገባቱንም አስታውቋል ኢትዮ ቴሌኮም የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸሙን ልሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል፡፡ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በሪፖርታቸው ላይ እንዳሉት ኢትዮ ቴሌኮም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 52 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል፡፡ እንዲሁም ድርጅቱ በሰጣቸው አገልግሎቶች 103 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማስገባቱንም ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል፡፡ የመንግሥትና የንግድ ተቋማት የክፍያ ስርዓታቸውን በቴሌ ብር እንዲፈፅሙ በማድረግ 30.5 ሚሊየን በላይ የቴሌ ብር ተጠቃሚዎችን ማፍራት መቻሉም ተገልጿል፡፡ በአጠቃላይ በቴሌብር አማካኝነት ከ394 ቢሊየን ብር በላይ ግብይት መፈጸሙን ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል፡፡  በኢንተርኔት ላይ የተጣለው ገደብ ተቋሙን የሚመለከት ሳይሆን፤ በመንግሥት አካል የተጣለ ገደብ ስለሆነ ከሚመለከተው አካል በሚሰጥ ፍቃድ የሚነሳ…
Read More