25
Mar
የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻም በሁለት ወራት ውስጥ መሸጥ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች ከተባሉ ነጋዴዎች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል፡፡ እነዚህ “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች የተባሉ ነጋዴዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡ ካቀረቧቸው ጥያቄዎች መካከልም የደህንነት ችግሮች፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እጥረት፣ የግብር እፎይታ ማነስ፣ የብድር አቅርቦት እጥረት፣ የማያሰሩ ፖሊሲዎች መብዛት እና የፖሊሲዎች በፍጥነት መቀያየር ችግሮች እንዲሁም መንግስት ለኢኮኖሚው ተገቢውን ትኩረት አለመስጠት የሚሉት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸውም መንግስታቸው ባለፉት አምስት ዓመታት ኢኮኖሚውን ለማሻሻል የተደረጉ ጥረቶችን እና በቀጣይ የመንግስታቸው ትኩረቶች ዙሪያ አድርገዋል፡፡ ከተሰጡ ምላሾች መካከልም የግብር ጉዳይ አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያ ኢኮኖሚው…