Blog

የውጭ ሀገር ዜጎች ቤት እና መኪና መግዛት ሊፈቀድላቸው ነው ተባለ

የውጭ ሀገር ዜጎች ቤት እና መኪና መግዛት ሊፈቀድላቸው ነው ተባለ

የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻም በሁለት ወራት ውስጥ መሸጥ እንደሚጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ተናግረዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች ከተባሉ ነጋዴዎች ጋር በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል፡፡ እነዚህ “ታማኝ“ ግብር ከፋዮች የተባሉ ነጋዴዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ማብራሪያ እንዲሰጧቸው ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡ ካቀረቧቸው ጥያቄዎች መካከልም የደህንነት ችግሮች፣ የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት እጥረት፣ የግብር እፎይታ ማነስ፣ የብድር አቅርቦት እጥረት፣ የማያሰሩ ፖሊሲዎች መብዛት እና የፖሊሲዎች በፍጥነት መቀያየር ችግሮች እንዲሁም መንግስት ለኢኮኖሚው ተገቢውን ትኩረት አለመስጠት የሚሉት ዋነኞቹ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምላሻቸውም መንግስታቸው ባለፉት አምስት ዓመታት ኢኮኖሚውን ለማሻሻል የተደረጉ ጥረቶችን እና በቀጣይ የመንግስታቸው ትኩረቶች ዙሪያ አድርገዋል፡፡ ከተሰጡ ምላሾች መካከልም የግብር ጉዳይ አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያ ኢኮኖሚው…
Read More
ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ኢትዮጵያ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ሙሉ በሙሉ አገደች

ከወራት ማመንታት በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት በነዳጅ የሚሰሩ የግል አገልግሎት ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር እንዳይገቡ እገዳ መጣሉ ተገልጿል፡፡ መኪኖችን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ በማስመጣት ስራ የተሰማሩ ኩባንያዎች እንዳሉት ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማስገባት እንደማይችሉ እንደተነገራቸው ተናግረዋል። ከመካከለኛው ምስራቅ፣ ከአውሮፓና ደቡብ አፍሪቃ ያጓጓዟቸውን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ማስገባት እንደማይችሉ ከሶስት ሳምንት በፊት ተነግሯቸዋል። በእገዳው ሳቢያ ከፍተኛ መጉላላትና ኪሳራ እንደደረሰባቸው ባለጉዳዮቹ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል። ከሳምንታት በፊት የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ማገዱን ለፓርላማ አባላት ሲያስታውቅ የገንዘብ ሚኒስቴር በበኩሉ እገዳው ተገባራዊ እንደማይደረግና በዕቅድ ደረጃ ያለ መሆኑን ተናግሮ ነበር። ይሁንና ባለፉት ቀናት የተለየ ፍላጎት ላላቸው የልማት ፕሮጀክቶችና ለህዝብ ትራንስፖርት የሚውሉ ካልሆኑ በቀር በነዳጅ የሚሰሩ…
Read More
በኢትዮጵያ የወንዴ የዘር ፍሬ መለገስ እንደማይቻል ተገለጸ

በኢትዮጵያ የወንዴ የዘር ፍሬ መለገስ እንደማይቻል ተገለጸ

ከሰሞኑ በትግራይ ክልል ወንዶች የዘር ፍሬያቸውን ሴቶች ደግሞ እንቁላላቸውን መለገስ እንደሚቻል የሚያሳይ ዘገባ መሰራቱ ይታወሳል፡፡ ቢቢሲ አማርኛ እንደዘገበው ከሆነ መሰረቱን በትግራይ ክልል መዲና መቀሌ ከተማ ያደረገ አንድ የህክምና ተቋም የወንድ ዘር ፍሬያቸውን ለሚለግሱ 10 ሺህ ብር እንዲሁም እንቁላላቸውን ለሚለግሱ ሴቶች ደግሞ 30 ሺህ ብር እንደሚከፍል አስታውቋል፡፡ ይህ የህክምና ተቋም ልጅ መውለድ ያልቻሉ ሰዎችን ጥያቄ መመለስ የሚያስችል ህክምና መጀመሩን እና ለዚህም የተለያዩ መስፈርቶችን አስቀምቷል፡፡ የጤና ሚኒስቴርን በጉዳዩ ዙሪያ እንዳለው ኢትዮጵያ ከበጎ ፈቃደኞች በተለገሱ የዘር ፍሬዎች አልያም እንቁላል ልጅ እንዲወለዱ የሚፈቅድ ህግ እንደሌላት አስታውቋል፡፡ በሚኒስቴሩ የጤና እና ጤና ነክ ተቋማት እና ባለሙያዎች ቁጥጥር ስራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው ጸዳል ለአልዐይን እንዳሉት ኢትዮጵያ…
Read More
ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

ኢትዮጵያ በሳውዲ አረቢያ ያሉ 70 ሺህ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው ልትመልስ ነው

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮያውያንን ወደ ሀገራቸው እመልሳለሁ ብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ “በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለስ ሦስተኛ ምዕራፍ በሁለት ሳምንት ውስጥ ይጀምራል” ብለዋል። በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኘው ኢትዮያውያንን ለመመለስ የተቋቋመው ብሔራዊ ኮሚቴ በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለመመለስ በተዘጋጀው ዕቅድ ላይ መክሯል። የብሔራዊ ኮሚቴው ሰብሳቢ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ፤ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለሱ ሥራ በብሔራዊ ኮሚቴው ውስጥ የታቀፉት የፌዴራል ተቋማት እና የክልሎችን የጋራ ቅንጅት ይጠይቃል ብለዋል። ከወዲሁ አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በተሟላ ሁኔታ በፍጥነት መጠናቀቅ እንደሚገባቸውም አምባሳደር ብርቱካን ተናግረዋል። አምባሳደር…
Read More
በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት ከስድስት ሺሕ በላይ ሠራተኞች ሥራ ማቆማቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ምክንያት ከስድስት ሺሕ በላይ ሠራተኞች ሥራ ማቆማቸው ተገለጸ

ባሳለፍነው ዓመት ሚያዚያ ወር የፌደራል መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን መልሼ ለማደራጀት ወስኛለሁ ማለቱን ተከትሎ ነበር በአማራ ክልል ግጭት የተከሰተው፡፡ ይህ ግጭት ቀስ በቀስ እያደገ መጥቶ ወደ ጦርነት የተቀየረ ሲሆን የቀድሞው የክልሉ መንግስት በመደበኛ የክልሉ የጸጥታ ሀይል ህግ ማስከበር እንደማይችል እና የፌደራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ በደብዳቤ ጠይቋል፡፡ ይህን ተከትሎም ከሀምሌ 2015 ዓ.ም መጨረሻ ቀናት ጀምሮ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአማራ ክልል ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ የነበረ ሲሆን አዋጁ ለተጨማሪ አራት ወራት መራዘሙ አይዘነጋም፡፡ በዚህ ጦርነት ምክንትም ከስድስት ሺህ በላይ የሆኑ ሰራተኞች ስራ ማቆም እና ቤተሰቦቻቸውን መመገብ አለመቻላቸው ተገልጿል፡፡ የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው ከሥራ ውጭ የኾኑ ዜጎች፣ በግጭቱ ምክንያት…
Read More
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አምስት ኤርፖርቶችን እየገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አምስት ኤርፖርቶችን እየገነባ መሆኑን ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አምስት ተጨማሪ የአገር ውስጥ መዳረሻ ኤርፖርቶችን እየገነባ መሆኑን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ። አሁን ላይ አየር መንገዱ 136 ዓለም አቀፍ እንዲሁም 22 የአገር ውስጥ መዳረሻዎች እንዳሉት የጠቆሙት ስራ አስፈጻሚው ተጨማሪ የአገር ውስጥ መዳረሻዎችን ለማስፋት የያዘውን ዕቅድ ተከትሎ በአሁኑ ወቅት አምስት የአገር ውስጥ መዳረሻ ኤርፖርቶችን እየገነባ መሆኑን ተናግረዋል።  ኤርፖርቶቹ የሚገነቡት በሚዛን ቴፒ አማን፣ ያቤሎ፣ ጎሬ፣ መቱና ደብረ ማርቆስ መሆናቸውን ገልጸው፤ አራቱ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ወደ ሥራ እንደሚገቡ አስታውቀዋል። ይህም በአገር ውስጥ ያሉ ደንበኞች ፍላጎት ተከትሎ የሚተገበር መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ሌሎች መዳረሻዎችን ጥናት ላይ በተመሠረተ መልኩ ግንባታቸው እንደሚቀጥል ተገልጿል። በሌላ በኩል በሰሜን ኢትዮጵያ ለሁለት…
Read More
በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

በንግድ ባንክ ባንድ ሌሊት 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ዝውውር መፈጸሙ ተገለጸ

ንግድ ባንክ ባሳለፍነዉ አርብ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ባጋጠመዉ ችግር 25 ሺ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር መደረጉና 2.6 ቢሊየን ብር መንቀሳቀሱን አስታውቋል ባንኩ ገንዘብ የወሰዱ ሰዎችን ለመጠየቅና ገንዘቡን ለማስመለስ ግብረሀይል ያቋቋመ ሲሆን በባንኩ ዲጂታል መዋቅር ላይ በውስጥ አዋቂ የተፈፀመ ጥቃት ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ገምተዋል፡፡ ቅዳሜ ዕለት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል መዋቅር ላይ የተከሰተውን ግድፈት ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ አካላትን ለማደን ግብረ ኀይል መቋቋሙ ተገልጿል፡፡ ግብረ ሀይሉ ከብሔራዊ ባንክና ከንግድ ባንክ ባለሙያዎች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት የተካተቱበት ነው የተባለ ሲሆን ዓላማው ደግሞ በስድስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ከባንኩ ያለ አግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ማስመለስ እና ማጣራት ነው፡፡ ይሁንና ባንኩ በተባለው ሰዓታት ውስጥ የተወሰደበትን የገንዘብ…
Read More
አድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ለመጎብኘት 150 ብር መክፈል ግዴታ ነው ተባለ፡፡

አድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን ለመጎብኘት 150 ብር መክፈል ግዴታ ነው ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ ከ128 ዓመት በፊት ለተካሄደው የጸረ ቅኝ ግዛት ትግል ድል ያደረገችበት የአድዋ ድል ሙዚያምን ከሶስት ሳምንት በፊት በአዲስ አበባ በይፋ ማስመረቋ ይታወሳል፡፡ ከ4 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ይህ ሙዚየም ከነገ መጋቢት ስድስት ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል፡፡ በዚህም መሰረት ይህንን ሙዚየም ለመጎብኘት በግለሰብ ደረጃ 150 ብር መክፈል ግዴታ ሲሆን ለተማሪዎች 75 ብር እንዲሁም ለልዩ ልዩ ጎብኚዎች ደግሞ 500 ብር ዋጋ ተተምኖለታል፡፡ ጎብኚዎች ሙዚየሙን መጎብኘት የሚችሉት ከጠዋት 2:30 እስከ አመሻሽ 11:30 ሰዓት ድረስ እንደሆነም ከመታሰቢያ ሙዚየሙ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል፡፡ ለሙዚየሙ ከተቀመጡ ማስታወሻዎች መካከል ለድሉ አስተዋጽኦ ያደረጉ የጦር መሪዎች መታሰቢያ ሀውልት እና ተቋማት ስያሜ ባለፈ የራሱ ሙዚየም…
Read More
ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በቱኒዚያ በተካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ የክፍለ አህጉራዊ ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ክፍለ አህጉራዊ የፍጻሜ ውድድር ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በቱኒዚያ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያን ወክለው ከተወዳደሩት መካከል በኮምፒውቲንግ ትራክ (Computing Truck) የተወዳደሩት የሶስት ተማሪዎች ቡድን ሞሮኮ እና ቱኒዚያን ተከትለው ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። በጠቅላላ ውድድሩ ከኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዝያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና ሞሮኮ የተውጣጡ 90 ተማሪዎች በተለያየ የውድድር ዘርፍ ተሳታፊ ሆነዋል። በውድድሩ ሶስተኛ ደረጃን የያዙት ተማሪዎች የሁዋዌን ዘመናዊ ስልክ የተሸለሙ ሲሆን የተቀሩት 6 ተማሪዎች በተሳትፏቸው የሁዋዌ ታብሌቶችን ተሸልመዋል። ኩባንያው ለተማሪዎቻቸው ድጋፍ ላደረጉ መምህራንም እውቅና ሰጥቷል። እነዚህ ሦስት ተማሪዎች ሁለቱ…
Read More
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የድምጻዊ አማኑኤል ሙሴ (ዝናር ዜማ) አልበምን ስፖንሰር አደረገ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የድምጻዊ አማኑኤል ሙሴ (ዝናር ዜማ) አልበምን ስፖንሰር አደረገ

ሰዋሰዉ መልቲሚዲያ እና ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ በሙዚቃዉ ዘርፍ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል። ከ100 በላይ አንጋፋና ወጣት ድምፃዉያንን እና ሙዚቀኞችን ያስፈረመው ሰዋሰዉ መልቲሚዲያ እና ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በሙዚቃ አልበሞች እና በሁነቶች ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተፈራርመዋል። ከሰዋሰዉ ድምፃዉያን መካከል አንዱ የሆነዉ እና ከፋሲካ ፆም በኋላ የሚለቀቀዉን የአማኑኤል ሙሴ አልበም ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የስፖንሰርሺፕ ድርሻዉን ወስዷል። በዝናር ዜማ የድምፃዉያን ስብስብ እራሱን ከህዝብ ጋር ያስተዋወቀዉ አማኑኤል ሙሴ  ‘’ጥቁር ዉሃ’’ የተሰኘዉ አልበሙም በሳፋሪኮም አጋርነት በሰዋሰዉ አፕ እንደሚለቀቅ ተገልጿል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከአማኑኤል ሙሴ በተጨማሪ ተስፋ የሚጣልባት ወጣት ሴት ድምፃዊ አልበምን ስፖንስር እንደሚያደርግ የተነገረ ሲሆን የድምፃዊቷን ማንነት ግን በቅርቡ ይፋ ይደረጋል ተብሏል። ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙዚቃ አልበምን ስፖንሰር ሲያደርግ የአሁኑ…
Read More