ICT

ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በቱኒዚያ በተካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ የክፍለ አህጉራዊ ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ክፍለ አህጉራዊ የፍጻሜ ውድድር ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በቱኒዚያ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያን ወክለው ከተወዳደሩት መካከል በኮምፒውቲንግ ትራክ (Computing Truck) የተወዳደሩት የሶስት ተማሪዎች ቡድን ሞሮኮ እና ቱኒዚያን ተከትለው ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። በጠቅላላ ውድድሩ ከኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዝያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና ሞሮኮ የተውጣጡ 90 ተማሪዎች በተለያየ የውድድር ዘርፍ ተሳታፊ ሆነዋል። በውድድሩ ሶስተኛ ደረጃን የያዙት ተማሪዎች የሁዋዌን ዘመናዊ ስልክ የተሸለሙ ሲሆን የተቀሩት 6 ተማሪዎች በተሳትፏቸው የሁዋዌ ታብሌቶችን ተሸልመዋል። ኩባንያው ለተማሪዎቻቸው ድጋፍ ላደረጉ መምህራንም እውቅና ሰጥቷል። እነዚህ ሦስት ተማሪዎች ሁለቱ…
Read More
በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ሁዋዌ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ባካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተወዳደሩት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች የተሳተፉ  ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎች  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ ሴኪዩሪቲ፣ WLAN፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ AI፣ OpenEuler እና OpenGaussን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ  ተሳትፈዋል። በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች የራሳቸውን የፈጠራ ሃሳብ ይዘው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎቹ “የግእዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ መወዳደሪያ ይዘው ቀርበዋል፡፡ የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ…
Read More
ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

የቻይናዋ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሼንዘን ከተማ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድርን ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ታስተናግዳለች፡፡ በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች ወደ ቻይና ያቀኑ ሲሆን ለተወዳዳሪዎቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡ ውድድሩን ህዋዌ ያዘጋጀው ሲሆን በየሀገሩ በተካሄደ የማጣሪያ ውድድሮች ላይ አሸናፊ የሆኑ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ተማሪዎቹ በዚህ  ዓለም አቅፍ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ያቀኑት የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳትፈው በየደረጃው በአሸናፊነት በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያን በዚህ ውድድር ላይ የወከሉት ዘጠኙ ተማሪዎች  የተገኙት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች ነው። በውድድሩ ተማሪዎቹ  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን…
Read More