Huawei

አሲያ ኽሊፋ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

አሲያ ኽሊፋ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 ሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመርጣለች፡፡ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓመታዊ የስልጠና መርሃ ግብር፣ ከሁዋዌ ታዋቂ የማኅበራዊ ኃላፊነት ስራዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም ባለፈው ሳምንት የ2025 የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር አለም አቀፍ አምባሳደሮችን መርጦ አሳውቋል። ከተመረጡት 12 አምባሳደሮች መካከል በኢትዮጵያ የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የአራተኛ ዓመት የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ የሆነችው አሲያ ኽሊፋ ትገኛለች። ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓላማውን ያደረገው በዓለም ዙሪያ ያሉ ወጣት ተማሪዎችን በአጭር ጊዜ ስልጠና  የዲጂታል ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን አረዳዳቸውን ማሳደግ ነው። ለዚህም አጫጭር ስልጠናዎችን፣ ዓለም አቀፍ ውድድሮችን እና የተመራቂዎች ማህበር እንቅስቃሴዎች (አልሙናይ) ተሳትፎ እንዲጎለብት ይሰራል። የባህል ልውውጦች አስፈላጊነት እና የስራ ፈጣሪነት…
Read More
ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የዲጂታል ጉብኝት እያደረጉ ነው

ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በቻይና የዲጂታል ጉብኝት እያደረጉ ነው

ሶስት ኢትዮጵያውያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በሁዋዌ አዘጋጅነት ለስምንት ቀናት በሚቆይ የዲጂታል ጉብኝት እየተሳተፉ ሲሆን ጉብኝቱ በቻይና ሼንዘን ተጀምሮ ቤጂንግ ላይ የሚጠናቀቅ ይሆናል። ለተመረጡ የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ቴክ ፎር ጉድ “Huawei Seeds for the Future (SFTF) Tech 4 Good” ያለፈው ዓመት ሰልጣኞች የተዘጋጀው ጉብኝቱ ነሐሴ 26 ተጀምሮ እስከ ጳጉሜ 3, 2016 ዓ.ም ድረስ ይቀጥላል። ጉብኝቱ ለተማሪዎች የቻይናን ዲጂታል መልከዓ ምድር ለመቃኘት፣ የአይሲቲ ክህሎት እና የቴክኖሎጂ ጅምሮችን ለማዳበር፣ እንዲሁም ተማሪዎቹ ስለሚሰሯቸው ስራዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸው እና ከኢንዱስትሪ ኃላፊዎች ጋርም ውይይት እንዲያደርጉ ልዩ እድል ይሰጣል። ተማሪዎች በዚህ ስልጠና እንዲሳተፉ ለማድረግ የማጣራት ሂደትን ያለፉ ሲሆን ከ2023 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ቴክ ፎር ጉድ ፕሮግራም ተሳታፊዎች…
Read More
ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያኑ በሞሮኮ በተካሄደ የቴክኖሎጂ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቀቁ

የኢትዮጵያ ቡድን በሞሮኮ በተካሄደው የሁዋዌ ቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድርን በአንደኝነት አጠናቋል፡፡ የሁዋዌ ሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር “Huawie Seeds for the Future 2024” የቴክኖሎጂ ስልጠና መርሃ ግብር በሞሮኮ (ኢሳዉራ) ከሰኔ 26 እስከ ሐምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም ተካሂዷል። ይህ ስልጠና ከምስራቅ፣ ሰሜን፣ ምዕራብ እና መካከለኛው አፍሪካ የተውጣጡ 17 አገራትን አሳትፏል። ኢትዮጵያም ከስምንት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ 10 ተማሪዎችን በስልጠናው ያሳተፈች ሲሆን ከእነዚህ ተማሪዎች መካከል 5 ተማሪዎችን የያዘው የኢትዮጵያ አንድ ቡድን በሁዋዌ ቴክፎርጉድ ክፍለ አህጉራዊ ውድድር አንደኛ በመሆን አሸንፏል፡፡ ተማሪዎቹ በቴክ ፎር ጉድ ክፍለ አህጉራዊ (ግሎባል) ፕሮጀክት ከመወዳደራቸው በፊት የተለያዩ የቴክኖሎጂ ስልጠናዎችን ወስደዋል። ተሳታፊ ተማሪዎቹ በ28 ቡድኖች ተከፋፍለው ለውድድር የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን ያዘጋጁ…
Read More
ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ኢትዮጵያዊያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር ላይ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በቱኒዚያ በተካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ የክፍለ አህጉራዊ ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል። የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር ክፍለ አህጉራዊ የፍጻሜ ውድድር ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በቱኒዚያ ተካሂዶ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያን ወክለው ከተወዳደሩት መካከል በኮምፒውቲንግ ትራክ (Computing Truck) የተወዳደሩት የሶስት ተማሪዎች ቡድን ሞሮኮ እና ቱኒዚያን ተከትለው ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። በጠቅላላ ውድድሩ ከኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣ ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዝያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና ሞሮኮ የተውጣጡ 90 ተማሪዎች በተለያየ የውድድር ዘርፍ ተሳታፊ ሆነዋል። በውድድሩ ሶስተኛ ደረጃን የያዙት ተማሪዎች የሁዋዌን ዘመናዊ ስልክ የተሸለሙ ሲሆን የተቀሩት 6 ተማሪዎች በተሳትፏቸው የሁዋዌ ታብሌቶችን ተሸልመዋል። ኩባንያው ለተማሪዎቻቸው ድጋፍ ላደረጉ መምህራንም እውቅና ሰጥቷል። እነዚህ ሦስት ተማሪዎች ሁለቱ…
Read More
ኢትዮጵያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር የሚወክሉ ተወዳዳሪዎች ቱኒዝያ ገቡ

ኢትዮጵያን በአፍሪካ የአይሲቲ ውድድር የሚወክሉ ተወዳዳሪዎች ቱኒዝያ ገቡ

ዘጠኝ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በ8ኛው የሁዋዌ ክፍለ አህጉራዊ የአይሲቲ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው ለመወዳደር ቱኒዚያ ገብተዋል፡፡ በየዓመቱ የሚካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ8ኛ ጊዜና በአገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ6ኛ ጊዜ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እየተካሄ ይገኛል፡፡ የአገር አቀፍ ማጣሪያና ማጠቃለያ ውድድር ከተካሄደ በኋላ ዘጠኝ ኢትዮጵያውያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አገራቸውን ወክለው በቱኒዚያ በሚካሄደው 8ኛው የሁዋዌ አይሲቲ ውድድር 2023-2024 ክፈለ አህጉራዊ የፍፃሜ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ቱኒዚያ ይገኛሉ። በውድድሩ ከዘጠኝ አገሮች ከተውጣጡ 90 ተማሪዎች ጋር የሚወዳደሩ ሲሆን እነዚህም አገራት ኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ካሜሩን፣  ሴኔጋል፣ አልጄሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ሊቢያ፣ ግብፅ እና ሞሮኮ ናቸው። ለዚህ አመት ውድድር ከ1,000 በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን 280 ተማሪዎች ካሉበት ሆነው…
Read More
በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

በዓለም አቅፉ የአይሲቲ ውድድር ላይ የተሳተፉ ኢትዮጵያዊያን 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

ሁዋዌ ከግንቦት 16 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ባካሄደው የሁዋዌ አይሲቲ ዓለም አቀፍ ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው የተወዳደሩት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል። በውድድሩ ከ36 አገሮች የተውጣጡ 146 ቡድኖች የተሳተፉ  ሲሆን ኢትዮጵያውያኑ ተማሪዎች  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን በመሆን በፕራክቲካል ትራክ (ዳታኮም፣ ሴኪዩሪቲ፣ WLAN፣ ቢግ ዳታ፣ ስቶሬጅ፣ AI፣ OpenEuler እና OpenGaussን ያካትታል) ሁለት ቡድን እና አንድ ቡድን በኢኖቬሽን ትራክ  ተሳትፈዋል። በኢኖቬሽን ትራክ የተወዳደሩት ተማሪዎች የራሳቸውን የፈጠራ ሃሳብ ይዘው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎቹ “የግእዝ ፊደላት ክላሲፋየር” የተሰኘ መወዳደሪያ ይዘው ቀርበዋል፡፡ የሁዋዌ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሚስተር ሊዩ ጂፋን ተማሪዎቹ ባመጡት ውጤት መደሰታቸውን ገልጸው ድርጅቱ…
Read More
ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

ኢትዮጵያ በሼንዘኑ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድር ላይ በዘጠኝ ተወዳዳሪዎች ትወከላለች

የቻይናዋ የቴክኖሎጂ ማዕከል ሼንዘን ከተማ ዓለም አቀፍ የአይሲቲ ውድድርን ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ታስተናግዳለች፡፡ በዚህ ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች ወደ ቻይና ያቀኑ ሲሆን ለተወዳዳሪዎቹ የአሸኛኘት ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡ ውድድሩን ህዋዌ ያዘጋጀው ሲሆን በየሀገሩ በተካሄደ የማጣሪያ ውድድሮች ላይ አሸናፊ የሆኑ የዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ ተማሪዎቹ በዚህ  ዓለም አቅፍ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ያቀኑት የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ውድድሮች ላይ ተሳትፈው በየደረጃው በአሸናፊነት በማጠናቀቃቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ኢትዮጵያን በዚህ ውድድር ላይ የወከሉት ዘጠኙ ተማሪዎች  የተገኙት ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች ነው። በውድድሩ ተማሪዎቹ  እያንዳንዳቸው ሶስት አባላት ያላቸው ሶስት ቡድን…
Read More